~ የመንግሥቱ ጠቅላይ አቃቤ ህግ እሊህ የህሊና እስረኞች እንደሚፈቱ በራሱ የዜና አውታሮች እና በዓለም አቀፍ የዜና አውታሮች ካስለፈፈ በኋላ በፓርቲው ውስጥ በተፈጠረ አለመግባባትና በተለይም የህወሓት ደጋፊዎች እንዴት ተደርጎ ይፈታሉ ? ለምንስ በዚህ ወቅት ይፈታሉ ? እንዲያውም በሥራ አስፈፃሚው ስብሰባ ወቅት ያልተነሳ ጉዳይ ነው የሚል ጉትጎታ በመጀመራቸው ምክንያት መንግሥት ሃሳቡን ቀይሮ ተጠርጣሪዎቹን
የኅሊና እስረኞቹ ግን ” ንክች አናደርጋትም ፣ አንፈርማትምም ” መጀመሪያስ እኛ መች ፍቱን አልናችሁ ። ከፈታችሁ መፍታት ነው ። ያለበለዚያ ንኩት ብለው በአቋማቸው መጽናታቸው ተነግሯል ። በተለይ የአበበ ቀስቶ እናት በትናንትናው ዕለት ለአሜሪካ ድምጽ የሰጡት ቃለመጠይቅ አንጀት አርስ እንደነበር በሁሉም ኢትዮጵያዊ አድናቆት ተችሮታል ። የአበበ ቀስቶ እናት እንዲህ ነበር ያሉት፦
” መንግሥት የካቲት 1 እፈታለኹ ብሎ ለመላው ዓለም ፣ ለኢትዮጵያ ህዝብ ጭምር ተናግሮ በ2 እነሱን ተጠያቂ አድርጎ ግንቦት 7 ነኝ በሉ ብሎ ቃሉን ማጠፉ ያሳፍረኛል።
~አንፈርምም ባሉት
~ እኛም መስዋዕትነት ከፍለናል። 6 ዓመት ከ 6 ወር እስር ቤት በመመላለስ።
~
~
~ልጄ ቢሞት አላዝንም።እውነትን ይዞ ነው። ለሀገር መታገል ከአያት ቅድመ አያቶቻችን የመጣ ነው ። አዲስ ነገር አይደለም።” ነበር ያሉት የፖለቲከኛው አበበ ቀስቶ እናት ።
~ የእኚህን እናት ወኔ ስሰማ እኔ ጥፍሬ ውስጥ መደበቅ ነበር የቀረኝ ። ጀግና የጀግና እናት እኮ ታስታውቃለች ።
የነገውን ዐይተን ደግሞ ለተነገ ወዲያ እንጠይቃለን ።
~ በተለይ ለዋልድባዎቹ አባቶች ለእነዚያ መነኮሳት ለእነ አባ ገብረ ኢየሱስ ማንኛውም ኦርቶዶክሳዊ ድምጹን ከፍ አድርጎ ለማሰማት ይዘጋጅ ። እነ አቡነ ማትያስ እንደሁ ጉዳያቸው አይደለም ። ምክንያቱም ታሳሪዎቹ መነኮሳት ነገዳቸው ከዐማራ ስላልሆነ ግድ አይሰጣቸውም ። ክፉ የዘር በሽታ አምጥተውብን መከራ ያበሉናል ። መነኮሳቱ ገዳም አይፍረስብን ዋልድባ አይታረስብን ባሉ ነው ተይዘው ፍዳቸውን የሚበሉት። በጨለማ ቤትም የሚማቅቁት ። እናም የተዋሕዶ ልጆች እንዘጋጅ ። በኅብረት ድምጻችን ለማሰማት እንዘጋጅ ። በእነዚህ አባቶች ጉዳይ እስላም ክርስቲያን ሳንል በአንድነት ልንጮኽ ይገባል ።
የነገ ሰው ይበለን ። ብቻ ነገ ደግሞ ሌላ ጣጣ አምጥተው አንፈታቸውም ብለው እንዳያሳቅቁን ። መቼም እነሱ እንደሆነ መንገድ ካልተዘጋ ፣ እ የጎማ ጭስ ካልሸተታቸው ፣ የሰውም ደም ፈሶ ካላዩ የሚሰሙ አይነት ሰዎች አይደሉም ።
እባካችሁ እናንት ኢህአዴጎች እነ እስክንድርንም ሀተታ ፣ ገተታ ሳታበዙ ፍቷቸው ። እነ በቀለ ገርባን ለመፍታት ጋሽ እሸቱ እንዳለው ” ወላ የተሃድሶ ስልጠና የለ፣ ወላ ችሎት መድፈር ዝባዝንኬ የለ፣ ወላ የይቅርታ ቦርድ ስብሰባ የለ ፣ ወላ ኦነግ ነኝ ብለህ ፈርም የለ ፤