ኦህዴድ ይህን በማድረጉ ስብእናቸዉ ከፍ ባሉ ሰዎች እየተመራ ለመሆኑ ማሳያ ነዉ!
– በዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ የኦህዴድ ዉሳኔ ተደስቻለሁ (እንደግለሰብ)
ኣንደኛዉ ዶ/ር ነጋሶ ዉስጣቸዉ ያሰገደዳቸዉን ነገር ኣደባባይ ኣዋሉት፡፡የፓርቲዉ ፕሬዝደንት እያሉ ከሚያራምዷቸዉ ሃሳቦች በተለየ የኦሮሞን ብሶት ብቻ ኣንጸባረቁ፤ኣንድነትንም በኣንዳንድ ጉዳዮች ስላልተስማሙ የምመራዉን ፓርቲ ኣላዉቀዉም ነበር ማለት ነዉ ኣሉ ተብለዉ የዉስጥ ቅሬታ ተፈጠረ፡፡ደጋፊዉን ለማንቀሳቀስ ትንሽ መታገስ ያሰፈልግ ነበርና ግዜ ስንጠብቅ ሁለተኛዉ ሁኔታ ተከሰተ፡፡ፓርቲዉ እንዲፈርስና ለግለሰቦች ተሰጥቶ እንዲፈርስ በዛ ሰፈር ሰዎች ተወሰነ፡፡እንደግለሰብ ብቻሳይሆን እንደኣመራር ሲያንገበግበኝ የኖረ ያልተሳካ ዉጥን ነበር፡፡
ኦህዴድ ይህን በማድረጉ ስብእናቸዉ ከፍ ባሉ ሰዎች እየተመራ ለመሆኑ ማሳያ ነዉ፡፡የተከበረም የተቀደሰም ተግባር ነዉ፡፡የስዪ ኣብረሃ ህግና የዶ/ር ነጋሶ ህጎች የስርኣቱን ቁንጮ ሰዎች ምቀኝነት፤ክፋት፤ተንኮል፤ጨካኝነት፤ትንሽነት….
ኦህዴድ ይህን ኣርጎት ከሆነ (ተጠራጣሪ እንድንሆን ስርኣቱ የፈጠረብን ችግር ነዉ) ኣሁንም ከፍ ከፍ እንዲል እየተመኘሁ እንደግለሰብ ለዉሳኔዉ ከብር ኣለኝ፡፡ካለደረገዉም ያደርገዉ ዘንድ ልባዊ ጥሪየ ነዉ፡፡ኣስበን ያልተሳካን ነገር የኦህዴድ ወንድሞቻችን በመፈፀማቸዉ ቢያንስ ለምስጋና ንፉግ መሆን የለብንም!!
የዶ/ሩ ስራ ሁሌም የሚዘከር፤የሚከበር ተግባር ነዉ፡፡የህዝብ ልጅ፤የግል ከብርና ጥቅም ብሎ ያልፈጠረባቸዉ ናቸዉ፡፡