ነፃ ጋዜጠኛ እንደሆነ ሲወሻክት የኖረው ዳንኤል ብርሃኔ (ትውልደ ኮካ) እና የዋዜማው አርጋው አሽኔ (ጎበዝ ተንታኝ) ትናንት በቪኦኤ ቀርበው ሰማይ ከምድር እንደሚርቅ የተራራቀውን የግንዛቤ ልዩነታቸውን ያስተጋባ ክርክር አድርገዋል፡፡ ዳንኤል ብዙ ቢያወራም አንድ የገባኝ ነገር ሳይኖር ብዙ ደቂቃዎች አለፉ፡፡ አወያዩ አሉላ ከሚያነሳው የክርክር ነጥብም ሆነ አርጋው ከሚያመጣው ጥሩ ትንታኔ ጋር በምንም የማይገናኝ ዘባሪኮም ይቀበጣጥራል – አይተ ዳንኤል፡፡እውነት የሌለው ሰው ትርጉም ያለው አረፍተነገር መስራት እንኳን እንደማይችል አስረጅ ነው የአይተ ዳንኤል ቅብጠራ! አርጋውን ማዳመጥ ስለፈለኩ ብቻ ዳንኤልን ማዳመጥ ነበረብኝ፤ አመት ያወራ የሚመስለኝ ዳኤል በመሃል አንድ አስደንጋጭ ነገር ተናገረ “የኢትዮጵያ ህዝብ ፖለቲካ አይጨንቀውም ቤቱን ካልተቀማ በቀር” ብሎ ቁጭ አለ! ምን ማለቱ ነው ???????አይምሮ የጎደለው መሰለኝ! አሁን ከኢትዮጵያ ዳር እስከዳር “ዳውን ዳውን ወያኔ” እያለ ያለው የሳኦቶሜ ህዝብ ኢትዮጵያውስጥ ጎራ ብሎነው ተብሎ ነው እንዴ በትውልደ ኮካዎች የሚታመነው? ወይስ ይሄ ሁሉ ህዝብ ቤቱን ተቀምቶ ነው በአፈሙዝ ላንቃ ሥር ቆሞ አምባገነንን እየተጋፈጠ ያለው ?!
ሆድ/ስልጣን ከጭንቅላት ስቦት አሽከርነትን ጌጥ አስመስሎ የሚያሳየው ኮካ በማጠራቀም የማይታማው ደግሞ ዝነኛው ብዓዴን ነው፡፡ አለምነው መኮንን፣ይናገር ደሴ፣ተፈራ ደርበው፣ንጉሱ ጥላሁን፣ገዱ አንዳርጋቸውን የመሰሉ ወዶገቦች ተጠቃሽ ናቸው፡፡ ከነዚህ አንዱ ንጉሱ ጥላሁን በትናንቱ የሁለት ሰዓት ዜና ብቅ ብሎ “በወልዲያ እና አጎራባች ከተሞች የሚደረገው ድርጊት የአካባቢውን እውነታ አይወክልም” ሲል እውነታውን የሚወክለው የእሱ ወዶገባነት፣ዛሬ ሌላ ነገ ሌላ የመዘባጠር ወናፍነት፣ እውነትን ሸምጥጦ ክዶ እንደዘርዛራ ወንፊት ሃሰት ማፍሰስ ነው ማለት ነው! እውነት ለመናገር እውነታውን የማይወክለው የውርጃው ብአዴን ውሽከታ እንጅ የህዝብ ብሶት አይደለም፡፡ በጌቶቹ ዘንድ ከዓለምነው መኮንን በልጦ ለመገኘት እንደዝንጀሮ እግር እየለካ ያለው ንጉሱ ጥላሁን የሚባል ጉድ ተኩሰው ከሚገድሉት እኩል ሰውን እያቆሰለ ያለ መርዘኛ እንደሆነ ሊታወቅ ይገባል፡፡ እጅግ በሚያበግነው የትናንቱ ንግግሩ የአማራ ህዝብ በዘር ብቻ ትግሬዎችን እያጠቃ እንደሆነ በገደምዳሜ ተናገረ፡፡ይህን ሲል በቆመለት ህዝብ የፖለቲካ ኪሳራ የአሽከርነቱን ልቀት ለጌቶቹ ማስመዝገቡን እንጅ የጎሳ ጭትን ዘር መበተኑን የካድሬ ግንዛቤው የሚነግረው አይመስለኝም፡፡ ለመሆኑ በመላው ወሎ የሚኖር ትግሬ ስንት ነዉና ስንቱ በትግሬነቱ ብቻ ተጠቃና ነው ይህን የሚያወራው? እንዴት ያለ ራስን መናቅ ነው እንዲህ ባለው የአሽከርነት ትቢያ የሚያንፏቅቅ????!!!!!