ወያኔ 26 አመታት ሙሉ በኢትዮቶጵያ ህዝብ ላይ በወሰደዉ ወንጀለኛ እርምጃ ይስማማሉ::ይባስ ብለዉም ወያኔ እንደሚለዉ ሁሉ ኢትዮጵያ የምትባል ሀገር በተረት ተረት የተፈጠረች: በቅኝ ግዛት የተሰበሰበ ህዝብ ያላት ሀገር ናት ብለዉ ይሰብካሉ:: ልባቸዉ በከፍተኛ ጥላቻ ከመሞላታቸዉ የተነሳ ከነሱ ጎሳ ዉጭ የሚያልቀዉ ሰዉ አያስጨንቃቸዉም::ነገ ተያይዞ የኢትዮጵያ ህዝብ የሚመሰግበት የእርስ በርስ የጎሳ ጦርነት ሀሴት ያጭርላቸዋል::ልባቸዉ ግማሽ ጥቁር እና ግማሽ ብርሃን ነዉ::ሆኖም ፍጹም ፈሪዎች እና አድር ባይ ናቸዉና ዛሬ የያዙትን አቋም ነገ ለመለወጥ ፈቃደኛ ናቸዉ::
እነዚህ ሀይሎች በድርጅት ስብስብ ትንታኔ ሲቃኙ ዝርዉ ናቸዉ::አንድ ድርጅት ዉስጥ አታገኛቸዉም::ወይም ደግሞ በአንድ አካባቢ አታገኛቸዉም::ዉጭ ሀገር ወይም ሀገር ቤት ሊሆኑ ይችላሉ::ግን አንድ የሚያሰባስባቸዉ ባህሪ ወያኔ እና ወያኔአዊ አሰራር በጣም ይመቻቸዋል::ፍትህ እና እዉነት ለነሱ ቦታ የለዉም::መደባቸዉም ሲጠና አንድ ነዉ::ወያኔነት::
ወያኔ ሊወድቅ የተንገዳገደ ሲመስላቸዉ ሰለሽግግር መንግስት ወይም ስለ እርቅ አለዚያም ከወያኔ መሃል ተነስቶ ወያኔን ስለሚጥለዉ ጀግና ይሰብካሉ::ልክ ግር ግሩ ሲያልፍ የኢትዮጵያ ህዝብ ሰቆቃ እና መከራ ይረሳቸዉ እና በጀርባቸዉ ለጥ ብለዉ እየተኙ ከወያኔ ጋር የፖለቲካ ድሪያቸዉን ዉስጥ ዉስጡን ያቀልጡታል:: ወያኔ ጉዳዮች እና ስብሰባዎች ላይ በኦህዴድነት: በብአዴንነት : በደህዴነንት ወይም በሆነ ፓርቲ ጥላ ስር አለዚያምም በሆነ ሲቪል ማህበር ስር ተወሻሽቀዉ ከወያኔ ምናምንቴ እና ርኩስ ሀገር የማጥፋት ሴራ ጋር ሲተባበሩ ይገኛሉ:: እናም ለምን ተብለዉ ሲጠየቁ ያለማፈር “ፖለቲካ ፍሌክሲብል መሆን ይጠይቃል::ድርቅ አትበሉ::አክራሪ አትሁኑ” ይሉሃል::ያንተን ጀግንንተ በነሱ ጭቃ ባንዳነት አኮስሰዉ እነሱ ባንተ ላይ የስነልቦና የበላይነት ሊያሰፍኑ መሆኑ ነዉ::
እነዚህ ሰዎች አንድ አስደናቂ እና ታላቅ የማጭበርበር ተሰጥኦ አላችዉ::በኢትዮጵያ ሰማይ ስር ለዉጥ የመጣ ከመሰላቸዉ የለዉጡ አካል በፍጥነት ይሆናሉ::በጣም ሳያፍሩም ለዉጡ ከወያኔ ከራሱ እንደሚመጣ ጭመር ይሰብኩሃል::እነሱ ሚሊዮኖች ስለሚደርስባቸዉ ነገር ጉዳያቸዉ አይደለም::
በአጋጣሚ እንቅ አድርገህ የያዝካቸዉ እንደሆነ ግን እጅግ በጣም አስገራሚ እና ታላቅ መስዋዕትነት እየከፈለ ያለዉን ተቃዋሚ ያሙልህ ይጀምራሉ::አሜታቸዉን ሲደመድሙም እንዲህ ይሉሃል::
“በተቃውሚ ተስፋ ቆርጠን ከወያኔ ማህጸን ለዉጥን ብንጠብቅ ልንወቀስ አይገባም” ይሉሃል ::ይባስ ብለዉም አንተም አብረህ ከነሱ ጋር ከወያኔ ማህጽን ለዉጥ እንድትጠብቅ ይጎተጉቱሃል:: ሀያ ስድስት አመታታ የኢትዮጵያ ህዝብ በዚህ መሰሉ ድራማ ዉስጥ አልፏል:: የሰሞኑ ድራማም የነዚህ ድኩማን ሀይላት ተባባሪነትን ባያገኝ ኖሮ እንዲህ በርካታ መደናገሮችን አያስከትልም ነበር::ሆኖም የኢትዮጵያ እዉነተኛ ጀግኖች በማንም የባንዳ ሀሳብ ተወዣብረዉ አያዉቁም::ሽህ አመት የተዋጋ ህዝብ: ህሽ አመት በምድር ላይ የኖረች ኢትዮጵያ በስዉር ጀግኖቿ ልዩ የማይናወጽ ትግል ብሎም በእግዚአብሄር ታምና ጭምር ነዉ እንጅ ፈተናት ከዘመናት እስከ አዝማናታ ተለይቷት አያዉቅም::: እንደ ወያኔ እና እንደ ወያኔ ተባባሪ ሀይላት ቢሆንም እማ ኢትዮጵያ ጠፍታ አልነበር?
ለጊዜው ኢትዮጵያ ጀግኖቿ በጨለማዉ ዉስጥ እየተጓዙ ስለሆነ የሀገሪቱ ጀግኖች የማያዩዋቸዉ ይመስላቸዋል::በጨለማ ዉስጥ የሚመላለሰዉ ጀግና እና በመከራ ዉስጥ የወደቀዉ ህዝብ ግን በደንብ ያዉቃቸዋል::እራቁታቸዉን አቁሞ ይመረምራቸዋል::በህዝቡ እና በጀግና መሃከል እየገቡ እነዚህ አድር ባይ ሀይሎች ግን በርካታ የብተና ስራ ስለሚያከናዉኑ የትግል ጉዞዉ ሊረዝም ችሏል::ግን ጉዟችን ረዥም ትግላችንን መራራ የሚሉ ጀግኖች በጨለማዉ ዉስጥ በጥንቃቄ መመላለሳቸዉን አላቆሙም:: እዉነትም ጉዞዉ ረዥም ትግሉም መራራ እንጅ አስመሳዮች እንደሚሉት ወያኔን ለመንቀል ከወያኔ ዉስጥ የሚነሱ ወንጀለኛ ሀይሎች የኢትዮጵያን ህዝብ ከባንዳዉ የወያኔ ስርአት በቀላሉ ነጻ አያወጡትም::
እናም በጥንቃቄ ስትመረምራቸዉ ወያኔ ለሃያ ስድስት አመታት በኢትዮጵያ ህዝብ ጫንቃ ላይ እንዲጨፍር ዋና ባለድርሻዎች እነዚህ መሆናቸዉ ግልጽ ነዉ::ከፍተኛ ዋጋ እየከፈለ ያለዉን ተቃዋሚ አጣጥለዉ ጸረ ኢትዮጵያዉያን ወያኔዎችን ወይም የወያኔ አሽከሮችን ያነግሱልሃል:: ከእነዚህ ፈጽመህ እራቅ::በተለይ በሞቀበት የመተባበር አይነት ባህሪ ካለህ በቀላሉ እንደሚያሳስቱህ አዉቀህ እንዲዝህ አይነት ሀይላት መረብ ዉስጥ እንዳትገባ በደንብ መርምራቸዉ::