ሃብታሙ አያሌው እና ያሬድ ጥበቡ
♦የኦህዴድና የብአዴን ፓርላማ ተቀማጮች ሃይለማሪያምን ሃገሪቱ የገባችበትን ትርምስ በተመለከተ ማብራሪያ እንዲሰጥ አዘዙት!
♦የኦህዴድና ብአዴን የፓርላማ ተቀማጮች ከድርጅቶቻቸው ጋር ስብሰባ ተቀምጠው አቋም ይዘዋል። የለማና የነገዱ ቡድን የፓርቲወቻቸውን ሙሉ ድጋፍ እንዳገኙ ይህ ይፋ አድርጎታል።
♦ለጥያቄያቸው መልስ ሳያገኙ መደበኛ ስብሰባ አናደርግም ብለዋል! የፓርቲወቻቸው ትእዛዝ ወርዶላቸዋል።
♦ህወሃት እና ገሚሱ ደህዴን በአንድ በኩል ብአዴንና ኦህዴድ በሌላ በኩል የሞት ሽረት እሽቅድምድም ገብተዋል። ብአዴንና ኦህዴድ የፓርላማ አብላጫ መቀመጫ ስላላቸው ወያኔ ትልቅ ስጋት ውስጥ ገብቷል።
♦ይህ ክንውን የኢህአዴግ ስራ አስፈፃሚ ፍጥጫ የተሞላበት ስብሰባ ጎን ለጎን እያደረገ በሚገኝበት ወቅት በመሆኑ ትርምሱን አባብሶታል!
የሪፖርተር ጋዜጣ ይህን ትርምስ ይፋ አድርጎታል። በኢህአዴግ ዘመን እንዲህ ያለ ክስተት ታይቶ አይታወቅም። አዲስ አበባ የለውጥ ማእበል እየናጣት ነው።
——