ከሁለት አመት በፊት ፖሊሶች የተቃውሞ ሰልፉን በኃይል ለመበተን ያደረጉት ጥረት ከሳምንት በኋላ ፈፅሞ ታይቶ በማይታወቅ መልኩ ከ50ሺህ በላይ የወሊሶ ከተማ ነዋሪዎች ለአመፅና ተቃውሞ አደባባይ ወጡ። በዚህ ምክንያት፣ በዜጎች ሕይወትና ንብረት ላይ ከፍተኛ ጉዳት ደረሰ። ከከተማዋ አልፎ በመላው ኦሮሚያ የፀጥታና አለመረጋጋት ችግር ተፈጠረ። በመጨረሻም በአስቸኳይ ግዜ አዋጅ አማካኝነት ህዝቡና ሀገሪቱ በወታደራዊ ቁጥጥር ስር ወደቁ።
ባለፈው ሳምንት የተካሄደው የተቃውሞ ሰልፍ ግን ፍፁም ሰላማዊ ነበር። ከጠዋቱ 2፡00 ሰዓት ላይ የተጀመረው የተቃውሞ ሰልፍ ከ15ሺህ በላይ ሰዎችን ተሳትፈውበታል። ነገር ግን፣ ከቀኑ 7፡00 ሰዓት ላይ ግን ሁሉም ነገር ተጠናቅቆ ሰዎች በሰላም ወደ መደበኛ ሥራቸው ተመልሰዋል። በሕይወትና ንብረት ላይ የደረሰ ጉዳት የለም። ከሁለት ዓመት በፊት የተካሄደውን የተቃውሞ ሰልፍ ፖሊሶች በኃይል ለመበተን ባይሞክሩ ኖሮ ዛሬ ከደረስንበት ደረጃ አንደርስም ነበር። በወቅቱ “
“ከዛሬ 50 አመት በፊት እንደነበረው ሁሉ፣ የተማሪዎችን እንቅስቃሴ በኃይል ለመበተን የሚደረግ ጥረት ሁኔታውን ይበልጥ ከማባባስ የዘለለ ሚና የለውም። ተመሳሳይ እንቅስቃሴ በተካሄደ ቁጥር ፖሊስ የተለመደ የኃይል እርምጃ በመውሰድ ነገሩን ከማባባስ ይልቅ ዋና ተግባሩ በሆነው የሰውና የንብረትን ደህንነት በማስከበር ላይ ትኩረት አድርጎ ቢሰራ የተሻለ ነው። የመንግስት ኃላፊዎችም በበኩላቸው የተነሳውን ተቃውሞ፣ ሃሳብን በነፃነት የመግለፅ መብትን በሚጥስ መልኩ የኃይል እርምጃ በመውሰድ አቋራጭ መፍትሄ ከመፈለግ ይልቅ የተነሳውን ጥያቄ በአግባቡ ተቀብለው ምላሽ ለመስጠት ጥረት ማድረግ አለባቸው።”
ከላይ በተጠቀሰው መሰረት፣ እንዲሁም ባለፈው ሳምንት በወሊሶ ከተማ ከታየው ሰላማዊ ሰልፍ አንፃር፣ የተቃውሞ ሰልፉን ወደ ሁከትና ብጥብጥ የሚቀይሩት ሰልፈኞች፥ ፖሊሶች ወይም ማንነታቸው ያልታወቁ ፀረ-ሰላም ኃይሎች አይደሉም። ከዚያ ይልቅ፣ ሁከትና ብጥብጥ የሚነሳው በፖለቲካ መሪዎች የተሳሳተ ግምትና ውሳኔ ምክንያት ነው።
ከሁለት አመት በኦሮሚያ አመፅና ተቃውሞ ሲቀሰቀስ የኢትዮጲያ መንግስት
ለሁለት አስርት አመታት “
ይህን እውነታ ተቀብሎ ተገቢ ምላሽ መስጠት የተሳነው ቡድን አንዴ “ኦነግና ግብፅ” ሌላ ግዜ “ህቡዕ ድርጅት” እያለ ሲቃዥ ይውላል እንጂ የሕዝቡን የነፃነት፥ እኩልነትና ፍትሃዊ ተጠቃሚነት ጥያቄ ማስቆም አይችልም። “የማሪያምን ብቅል የበላ ሲለፈልፍ ያድራል” እንደሚባለው ሁሉ የኦሮሞን ሕዝብ መብትና ነፃነት የበላ መንግስት ኦነግ፥ ግብፅ፥ ህቡዕ፥…እያለ ሲለፈልፍ ያድራል!