ተሜ ደጋግሞ “ህወሓት የአንድ ፀሐፊን ብዕር ከባታልዮ ጦር በላይ ይፈራል ፍርሃቱ ልክ የለውም ” ይለኝ ነበር። የዛ ፍርሐት ልክ ይህው ለሶስት አመታት በእስር እንዲማቅቅ ምክንያት ሆነው። በመሰረቱ ከልቤ እንደማምንበት እንደ ፕሮፌሰር መስፍን አባባል “ህገ አራዊታቸው” እንኳን በተፃፈው መንገድ ቢሰራ ተሜ ሐምሌ ጥቅምት 25 ቀን 2010 ዓ/ም ከእስር መፈታት ነበረበት። ምክንያቱም የመለስን ሞት ተከትሎ ለአንድ ሳምንት ታስሮ ነበር ። የተፈረደበት በዚያው ክስ ስለሆነ ያ ሊደመር ይገባ ነበር። ነገር ግን አልሆነም ተሜ አመክሮ ተከልክሎም እንደገና ቦነስ እየታሰረ ነው። እነ እንቶኒ የሚናኙባት ኢትዮጵያ ለተሜ የምትፋጅ እሳት ሆነች። ህወሓትን ለመክሰስ ሺህ ምክንያት አለኝ የምለው ለዚህ ነው። የሚሟገቱለት ጠየቆቹም ምክንያት እንዳላቸውም በደምብ ይገባኛል። እንኳን ለግዕዝ በቀረበው ትግሬኛ በኮሪያኛ ሲናገሩም እረዳቸዋለዎ።
ህወሓት የአንድ ፀሐፊን ብዕር ከባታልዮ ጦር በላይ ይፈራል ፍርሃቱ ልክ የለውም (ሃብታሙ አያሌው)
Filed in: Amharic