1) በወያኔዎች መሪነትና ልዩ ፖሊስ በተባለው ቅጥረኛ ነፍሰ ገዳይ ወታደሮች ኦሮሚያ ላይ እየተካሄደ ያለው ወረራና ግድያ በአስቸኳይ እንዲቆም ለማሳሰብ፤
2) ወያኔዎች ወንድማማች የሆኑትን የኦሮሞና የሶማሊ ህዝቦችን ለማጋጨት የሚያደርገውን እኩይ ተግባር ለመቃወምና የሁለቱ ህዝቦች ወንድማማችንነት እና አንድነት በዚህ ዓይነቱ እኩይ የወያኔዎች ተግባር ፈጽሞ ሊስተጋጋል እንደማይችል ግልጽ መልዕክት ለማስተላለፍ፤ ብሎም የኦሮሞ ህዝብ ለሶማሊ ህዝብ ያለውን ፍቅር፣ ወንድማማችነትና አጋርነት በዛውም ለማሳየት፤
3) ወያኔ ከኋላ ሆኖ ህዝብን ለማጋጨት ከሚያደርገው ከዚህ ዓይነቱ አደገኛ ድርጊት እንዲቆጠብ ለማስጠቀቅ ይሆናል።
ሰልፉ ፍጹም ሰላማዊ ይሆናል። ሰልፉን በሁሉም የኦሮሚያ አካባቢዎች ያሉ ቄሮዎች በግንባር ቀደምትነት የሚያስተባብሩት ሲሆን የየአካባቢዎቹ የሃገር ሽማግለውዎች ይመሩታል።
ስለሆነም በዚህ በመላው ኦሮሚያ ከላይ የተጠቀሱትን ሶስት ዓላማዎች አንግቦ ሊደረግ በታቀደው ሰላማዊ የተቃውሞ ሰልፍ ላይ በመጪው ሃሙስ ተሳትፎና ድጋፍ እንድታደርጉ ለሁሉም የኢትዮጵያ ህዝቦች አስተባባሪዎቹ በታላቅ አቅብሮት ጥሪ አስተላልፈዋል።