የአፓርታይድ ስርዓት በአለም የመጨረሻው መጥፎ ፖለቲካዊ ስርዓት ነው፡፡ አንዴ ከተተከለ በኋላ እሱን መንቀል እጅግ በጣም አስቸጋሪ ነው፡፡ ምክንያቱም፣ በደልና ጭቆና የሚፈፅመው የራሱን ርዕዮተ-አለም ወይም መርህ ተከትሎ ሳይሆን ከህዝብ በስተጀርባ ተደብቆ ነው፡፡ የደ.አፍሪካው
በመጀመሪያ “ሕወሃት ከሌለ የትግራይ ህዝብ የለም፣ የትግራይ ህዝብ ከሌለ ሕወሃት የለም” በሚል መፈክር የራሱን ህልውና ከህዝቡ ህልውና ጋር ፕሮፓጋንዳ አቆራኘ፡፡ ከዚያ በኋላ የደ.አፍሪካው አፓርታይድ ስርዓት በጥቁሮች ላይ ሲፈፅም የነበረውን በደልና ጭቆና በብዙሃኑ ኢትዮጲያዊን ላይ መፈፀም ጀመረ፡፡ የመብትና ነፃነት ጥያቄ የሚያነሱ ወገኖች በፓርቲ ወይም መንግስት ላይ ሳይሆን በህዝብ ላይ የተቃጣ ጥቃት እንደሆነ በመግለፅ ራሱን ከህዝቡ በስተጀርባ መደበቅ ጀመረ፡፡ በመንግስታዊ ስርዓቱ ላይ የሚነሳ አመፅና ተቃውሞ በፖለቲካዊ ስርዓቱ ላይ ሳይሆን በትግራይ ህዝብ ላይ እንደሆነ በመግለፅ የሚወክለውን ህዝብ በፍርሃት ማራድና ከሌላው የኢትዮጲያ ህዝብ ይነጥላል፡፡ ይህ ህዝብን ከህዝብ ያቃቅራል፣ ገዢው ቡድን ደግሞ የስልጣን ዘመኑን ያራዝማል፡፡
ይሄን ሁሉ የፃፍኩት ለምንድነው?
(ከዚህ ሁሉ በኋላ፣ “ይህ ፅሁፍ ለትግራይ ህዝብ ያለህን ጥላቻ ወይም ዘረኝነት ያሳያል” የሚለኝ ሰው ካለ፣ እሱ በተፈጥሮ የተሰጠውን አስተዋይ አዕምሮ