(ኢሳት ዜና ነሃሴ 18 ቀን 2009 ዓም)
ነፍሰጡር እናቶች፣ ታዳጊ ሕጻናቶችን ጨምሮ ካለምንም ተለዋጭ መኖሪያ ቤት ጎዳና ላይ እንዲጣሉም ተደርገዋል። ከሃያ በላይ እድሜያቸው ከ3 ወር እስከ 3 ዓመት የሚሞላቸው ሕጻናት ላለፉት አራት ቀናት በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ይገኛሉ። ታዳጊ ሕጻናቱ በአንድ መጋዘን ውስጥ ታግተው እንዳይወጡ ተደርገዋል።
ስደተኞች ሌሎች አገሮች እንዲቀበሉን አሻራችንን አንስታችሁልን ወደ ሌሎች አገሮች እንድንሄድ ይፈቀድልን ሲሉ የጣሊያንን መንግስትን ተማጽነዋል። ከሞቀ ቤታቸው ወጥተው ጎዳና ላይ ምጽዋት ተቀባይ መሆናቸው እንዳሳዘናቸው ጉዳተኞቹ አክለው ገልጸዋል።