ፈይሳ ሊሌሳ በሪዮ ኦሎምፒክ በተደረገው የማራቶን ሩጫ ውድ ድ ር 2:10:05 በማምጣት የብር ሜዳሊያ ለሃገሩ ኣስገኝቶኣል። ይህም ብቻ ኣይደለም፤ ፈይሳ ሊሌሳ በተገኘችው ኣጋጣሚ በኢትዮጵያ ውስጥ በኣምባገነኑ ስርዓት በየቀኑ በኣጋዚ ወታደሮች ለሚገደሉት፣ ለሚሰደዱት፣ ለሚታሰሩት ወገኖቹ ከ 42 ኪሎ ሜትር እልህ ኣስጨራሽና ኣድካሚ ውድድር በኃላ በድል ሲቀዳጅ ኣጋርነቱን እጁን በማጣመር ለዓለም ኣሳይቶኣል። ብቻውን ሮጦና ለድል በቅቶ ለብዙዎች ድምጽ መሆን የቻለ የወቅቱ ጀግናና ኣንበሳ፤ ፈይሳ ሊሌሳ።
ፈይሳ ሊሌሳ፤ የወቅቱ...አንበሳ!
Filed in: Amharic