>

መልካም ልደት! ናፍቆት እስክንድር ነጋ

Happy Burthday to Nafkot Eskindr Nega ቅዱስ ሃብት በላቸው

ዛሬ ቃሊቲ እስር ቤት በግፍ ታስሮ የሚገኘው የአይበሬው ወንድማችን የጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ አንድዬ ልጅ የናፍቆት እስክንድር የልደት ቀን ነው!! … ለነገሩ ናፍቆትሻም የተወለደው እዚያው ቃሊቲ ውስጥ ነውና ከውልደቱ ጀምሮ ታላቅ ታሪክ ያለው ልጅ ነው። እግዚአብሔር አምላክ ታላቅ ሰው እንደሚያደርገው ደግሞ እምነቴ ፅኑ ነው! ፀሎቴንም አላቋርጥም!! … ለማንኛውም ናፍቆትሻን መልካም ልደት እንበለው !! ደግሞም የነፃነት ቀን ቀርቧልና በቅርቡ እንደሻማ እየነደደ ለሌላው ብርሃን በመስጠት ላይ ያለው አባቱም ነፃ ወጥቶ፣ መጪው ልደቱን ከመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ጋር በታላቅ ፌሽታና ደስታ እንደምናከብረው ጥርጥር የለኝም!! ናፍቆትሻ በርታልን! ጎብዝልን! እደግልን!
ሞት ለወያኔ! ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ !!

Filed in: Amharic