ብዙ ሰዎች የተገነዘቡ አይመስለኝም እንጂ ችግሩ ቋንቋን (ማለት ትግርኛን) የትግርኛ ተናጋሪዎች ሞኖፖሊ (የብቻቸው) የማድረግ ጥረት ያለ ቢመስልም፣ ዋናውና ትልቁ አደጋ ሀሳብንም ቀለም እየቀቡ የሚቀበሉትንና የማይቀበሉትን ለመለየት መሞከሩ ነው፡፡
ይቺ ሴት በትግራይም ጉዳይ ይሁን በኢትዮጵያ ጉዳይ አስተያየት የራስዋን አስተያየት ሰጥታለች፤ ትርፋማ የሚሆነው ምን አለች? ምን አስተያየት አቀረበች? ነው እንጂ ወያኔን ተቃውማለች፤ የለም፣ አልተቃወመችም፣ የሚል ነበር፤ መቃወምም፣ መደገፍም መብትዋ መሆኑን ተቀብለን ከተቃውሞዋ ምን እንማራለን? ከድጋፍዋስ ምን እንማራለን? ለትግራይም ሆነ ለኢትዮጵያ (ለትግራይ የሚበጀው ለኢትዮጵያም ይበጃል፡፡)
ወያኔዎች፡– እውነት፣ እውነት እላችኋለሁ የእውነትን መስቀል ተሸክመው ከትግራይ ብቅ የሚሉ ሰዎች ነበሩ፤ አሉ፤ ይመጣሉ!!! ገብረ መድኅንን፣ አስገደን ከነልጆቹ፣ አብርሃን … እስከዘላለሙ አንረሳቸውም፡፡
በአደባባይ የተነገረው እውነት ውሸት ሆኖ ይከስማል ወይም እውነት ሆኖ ይጠበድላል [ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማሪያም]
Filed in: Amharic