>
5:13 pm - Tuesday April 18, 8902

''የሀጎስ ጌታነት የቶላ ዘበኝነት ሊያበቃለት ይገባል'' [ጃዋር መሐመድ]

Jawar Mohammed“እደግመዋለሁ የሀጎስ ጌታነት የቶላ ዘበኝነት ሊያበቃለት ይገባል። ይህ ዘረኝነት አይደለም። የጸረ ዘረኛ ስርዓት አቋም እንጂ። ዘረኝነት ( racism ) ትርጉሙ ምንድነው? ዘረኝነት ማለት አንድ ግለሰብ ወይንም ቡድን በሌላው ላይ ያለውን የ ጥላቻ/ንቀት አመለካከት በተቆጣጠረው ስልጣን ተጠቅሞ ሲጎዳ ነው (Racism is Prejudice plus power)። በዚህ ትርጉም ተመስርተን ዛሬ እትዮጲያ ውስጥ ባለው ተጨባጭ ሁኔታ ዘረኛ መሆን የሚችለው ስልጣን ላይ ያለው ቡድን ብቻ ነው። ሌሎች የ ጥላቻ (hate)፣ ንቃት ወዘት አመለካከት ሊኖራቸው ይችላል። ያንን አመልካከታቸውን በተጨባጭ ስራ ላይ ለማዋል የፖሊቲካ ስልጣን እስከሌላቸው ድረስ ዘረኛ ( racist) መሆን አይችሉም።
የትግሬ ገዢ ቡድን በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ የኦሮሞን ገበሬዎች እያፈናቀለ እራሱን እና የራሱን ቡድን ማደላደል የለበትም የሚለው አቋም የሚያስከፍችሁ ከሆነ፤ አሁንም ደግመዋለሁ። በቶላ አንጡራ ሀብት መሬት ላይ ሀጎስ ኢንቨስተር፣ ቶላ አሽከር እንዲሆን አይፈቀድም፤ ያንን እያስፈጸመ ያለው ዘረኛ ስርዓትም ሊወገዝ፣ ሊደመሰስ ይገባዋል!!
የዛሬዋ እትዮጲያ በትግሬ ገዢ ቡድን መዳፍ ስር መሆኗን ከዳችሁ ማሳመን ለምትፈልጉት ሂዱና መጀመሪያ የራሳችሁን ህሊና አሳምኑ።” Jawar Mohammed

Filed in: Amharic