>

ሰማያዊ እና ኦፌኮ በጋራ ለመስራት ተስማሙ

DR Merara And Semayawi Party

ነገረ ኢትዮጵያ

ሰማያዊ ፓርቲና የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረንስ (ኦፌኮ) በጋራ ለመስራት መስማማታቸውን የሰማያዊ ፓርቲ ምክትል ሊቀመንበር አቶ ነገሰ ተፋረደኝ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልፀዋል፡፡ ሁለቱ ፓርቲዎች ዛሬ ታህሳስ 5/2008 ዓ.ም ባደረጉት ስብሰባ በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ የጋራ መግለጫ በመስጠት፣ መንግስት የሚፈፅመውን የሰብአዊ መብት ጥሰት በመከታተል ለማጋለጥ እንዲሁም ሰላማዊ ሰልፍና ስብሰባዎችን በጋራ ለማካሄድ እንደተስማሙ ምክትል ሊቀመንበሩ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልፀዋል፡፡

የሰማያዊ ፓርቲ ብሄራዊ ምክር ቤት የፓርቲው ስራ አስፈፃሚ ከመድረክ ጋር እንዲሰራ በወሰነው መሰረት ዛሬ ከኦፌኮ ጋር በተደረገው ውይይት በሰማያዊ ፓርቲ በኩል ሊቀመንበሩ ኢ/ር ይልቃል ጌትነት፣ ምክትል ሊቀመንበሩ አቶ ነገሰ ተፋረደኝ፣ የድርጅት ጉዳይ ኃላፊው አቶ ጋሻው መርሻና የሴቶች ጉዳይ ኃላፊ ወ/ሮ መዓዛ መሃመድ ተገኝተዋል፡፡ በኦፌኮ በኩልም ሊቀመንበሩ ዶ/ር መረራ ጉዲና፣ ምክትል ሊቀመንበሩ አቶ ሙላቱ ገመቹ እና ፀኃፊው አቶ በቀለ ነገአ ተገኝተዋል፡፡ ሁለቱ ፓርቲዎች በቅርቡ በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ የጋራ መግለጫ እንደሚሰጡና የጋራ ግብረ ኃይል አቋቁመው የፖለቲካ ትግል እንደሚያደርጉም አቶ ነገሰ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልፀዋል

Filed in: Amharic