>
5:13 pm - Saturday April 19, 5023

የኢትዮጵያዊያኑ ስደተኞች ሰቆቃ ዛሬም ከወደ ደ/አፍሪካ ይጣራል [ታምሩ ገዳ]

“ይህ አስር ቤት ለእኔ በምድር ላይ ያለ ሴኦል ሆኖ ነው የሚታየኝ” የ 15 አመቱ ኢትዮጵያዊ እስረኛ

by Tamru Geda 15102015በተለያዩ ምክንያቶች ህይወታቸውን ለመለወጥ/ለማሻሻል በማለት ወደ ደቡብ አፍሪካ ለማቅናት ሲሉ በጎረቤት ማላዊ በኩል ለማቋረጥ የሞከሩ በርካታ ኢትዮጵያዊያን ሰደተኞች በፖሊስ ተይዘው የተፈረደባቸወን የገንዘብ እና የእስራት ቅጣት ቢጨርሱም በአሳቃቂው የማላዊ እሰር ቤት ወስጥ ፈዳቸውን እያዩ እንደሚገኙ የፈረንሳዩ የዜና ወኪል (አጃንስ ፈራንስ ፕሬስ ) እሮብ ጥቅምት 14 2015 አኤአ አ ዘግቧል።
“ለተሻለ ኑሮ ወደ ደ/አፍሪካ ለመሻገር የቋመጡት ኢትዮጵዊያን ሰደተኞች ምኞታቸው ቅዠት ሆነ። “ ያለው ዜና ዘገባው ከመዲናይቱ ሎላንግዊ 85 ኪሜ ርቀት ላይ የሚገኘው እና ለ 800 እስረኞች ተብሎ በተገነባው የዲደዛ እስር ቤት ውስጥ ወደ 2,650 የሚጠጉ እስረኞች ከእነዚህ መካከል 317 በላይ ኢትዮጵያዊያኖች ያለ በቂ ምግብ እና ውሃ አቅርቦት እየተሰቃዩ ይገኛሉ ብሏል።የ15 አመቱ ኢያሱ ታዲዮስ ባለፈው ሃምሌ ወር ከ 29 ጓደኞቹ ጋር ማላዊ ውስጥ ታሰረው በፍርድ ቤት የተጣለባቸውን የገንዘብ አና የእሰራት ቅጣት ቢፈጽሙም “ወደ አገራቸው የሚያጓጉዛቸ ተቋም በመታጣቱ ለተጨማሪ ሰቆቃ ተጋልጠዋል ተብሏል።እያሱ ሰለደረሰበት ሰቆቃ ሲናገር “ይህ እሰር ቤት ለእኔ በምድር ላይ ያለ ሲኦል ሆኖ ነው የሚታየኝ። ቀድሞ የነበረኝ ሕልም እና ተሰፋ ሁሉ እዚህ ላይ ተገቷል ። ከ 5 ጓደኞቼ ጋር የተጣለብን 62 ዶላር ቅጣትን ብንከፍልም እና እስራቱን ብንጨርስም እስከ አሁን ድረስ አልተፈታንም ። አሁን የምፈልገው ነገር ቢኖር ወደ አገሬ መመለስ ብቻ ነው ።” በማለት ሰውነቱ በደካም እና በረሃብ የጠወለገው ታዳጊው ወጣት ኢያሱ በማላዊው እስርቤት ውስጥ የደረሰበትን ሰቆቃ እና መጥፎ ገጠመኝ በመግለጽ “የድረሱልን” ጥሪውን አቅርቧል።
by Tamru Geda 15102015=2ባለፈው መሰከረም ወር በአሜሪካው የሰደተ ተመላሾች ደረጅት አማካኝነት 70 ኢትዮጵያዊያን ሰደተኞች ነፍሳችውን ብቻ አትርፈው ወደ አገራቸው በበጎ ፍቃደተኝነት የተመለሱ ሲሆን በአሁኑ ወቅት በእሰራት ላይ ያሉተን 317 ወገኖቻችንን ወደ ኢትዮጵያ ለማጓጓዝ በትንሹ የ አሜሪካ 200,000 ዶላር እንደሚያሰፈልግ ተገምቷል።የአለም አቀፉ ከሰደት ተመላሾች ድርጀት ተሰፋ የጠፋባቸው ኢትዮጵያዊያኑ ሰደተኞችን ወደ አገራቸው ለማጓጓዝ የበኩሉን ጥረት ቢያደረግም የአለማቀፉ ማህበረሰብ ወቅታዊ ትኩረቱ ወደ መካከለኛው ምስራቅ (የሶሪያ ሰደተኞች) ላይ በመሆኑ አትዮጵያዊያኑ ሰደተኞች አሰተዋሽ አጥተዋል ተብሏል ። የደርጅቱ ዋና ሹም የሆኑት ሚስስ ካትሪን ሳኒ በበኩላቸው “እነዚህ ማስኪን ነፍሳት ከአገራቸው /ከኢትዮጵያ / እርቀው እንደዚህ አይነቱ አሰከፊ ሁኔታ ውስጥ መውደቃቸው በእጅጉ ያሳዝናል” በማለት በኢትዮጵያዊያኑ ሰደተኞች ላይ እየደረሰ ያለው ችግርን በሃዘኔታ ለማስረዳት ሞክረዋል።
በዚህ አጋጣሚ አገሪቱ በኢኮኖሚዋ “አድጋለች፣ ተመንደጋለች፣ ሰላም እና መረጋጋት ዙሪያ ገባዋን ሰፈኖባታል” ከተባለ ለምን ቁጥራቸው ቀላል የማይባል ፖለቲከኞች ያልሆኑ ነገር ግን የወደፊቱ አገር ተረካቢ የሆኑ ሕጻናት እና ወጣቶች አስከፊውን የባህር እና የየብስ ጉዞ በማድረግ ለእንደዚህ አይነቱ እጅግ ዘግናኝ እና አሳቃቂ ችግር ይጋለጣሉ? ብለው የሚጠይቁ ወገኖች ተበራክተዋል።

Filed in: Amharic