“ይህ አስር ቤት ለእኔ በምድር ላይ ያለ ሴኦል ሆኖ ነው የሚታየኝ” የ 15 አመቱ ኢትዮጵያዊ እስረኛ
“ለተሻለ ኑሮ ወደ ደ/አፍሪካ ለመሻገር የቋመጡት ኢትዮጵዊያን ሰደተኞች ምኞታቸው ቅዠት ሆነ። “ ያለው ዜና ዘገባው ከመዲናይቱ ሎላንግዊ 85 ኪሜ ርቀት ላይ የሚገኘው እና ለ 800 እስረኞች ተብሎ በተገነባው የዲደዛ እስር ቤት ውስጥ ወደ 2,650 የሚጠጉ እስረኞች ከእነዚህ መካከል 317 በላይ ኢትዮጵያዊያኖች ያለ በቂ ምግብ እና ውሃ አቅርቦት እየተሰቃዩ ይገኛሉ ብሏል።የ15 አመቱ ኢያሱ ታዲዮስ ባለፈው ሃምሌ ወር ከ 29 ጓደኞቹ ጋር ማላዊ ውስጥ ታሰረው በፍርድ ቤት የተጣለባቸውን የገንዘብ አና የእሰራት ቅጣት ቢፈጽሙም “ወደ አገራቸው የሚያጓጉዛቸ ተቋም በመታጣቱ ለተጨማሪ ሰቆቃ ተጋልጠዋል ተብሏል።እያሱ ሰለደረሰበት ሰቆቃ ሲናገር “ይህ እሰር ቤት ለእኔ በምድር ላይ ያለ ሲኦል ሆኖ ነው የሚታየኝ። ቀድሞ የነበረኝ ሕልም እና ተሰፋ ሁሉ እዚህ ላይ ተገቷል ። ከ 5 ጓደኞቼ ጋር የተጣለብን 62 ዶላር ቅጣትን ብንከፍልም እና እስራቱን ብንጨርስም እስከ አሁን ድረስ አልተፈታንም ። አሁን የምፈልገው ነገር ቢኖር ወደ አገሬ መመለስ ብቻ ነው ።” በማለት ሰውነቱ በደካም እና በረሃብ የጠወለገው ታዳጊው ወጣት ኢያሱ በማላዊው እስርቤት ውስጥ የደረሰበትን ሰቆቃ እና መጥፎ ገጠመኝ በመግለጽ “የድረሱልን” ጥሪውን አቅርቧል።
በዚህ አጋጣሚ አገሪቱ በኢኮኖሚዋ “አድጋለች፣ ተመንደጋለች፣ ሰላም እና መረጋጋት ዙሪያ ገባዋን ሰፈኖባታል” ከተባለ ለምን ቁጥራቸው ቀላል የማይባል ፖለቲከኞች ያልሆኑ ነገር ግን የወደፊቱ አገር ተረካቢ የሆኑ ሕጻናት እና ወጣቶች አስከፊውን የባህር እና የየብስ ጉዞ በማድረግ ለእንደዚህ አይነቱ እጅግ ዘግናኝ እና አሳቃቂ ችግር ይጋለጣሉ? ብለው የሚጠይቁ ወገኖች ተበራክተዋል።