”በኢትዮጵያውያን ወገኖች ላይ በየስፍራው የሚደረገው የሰብኣዊ መብት ጥሰቶች የህወሃት/ኢህኣዲግ ውጤት ነውና የኖርዌይ መንግስት ለዚህ ኣፋኝና ገዳይ ስርዓት የሚያደርገውን ድጋፍ እንዲያቆም ሰልፈኞቹ ኣሳስበዋል።በመጨረሻም ይህ የኢትዮጵያ ስደተኞች ማህበር በኖርዌይ ያዘጋጀው ሰልፍ ከመጠናቀቁ በፊት ኣዘጋጅ ኮሚቴው የፖለቲካና የሃይማኖት መሪዎች ንግግር ኣድርገው የሰልፉ ፍጻሜ ሆኖኣል።ሰልፉ የተካሄደው እኩለ ቀን በስራ ሰዓት ላይ በመሆኑ ሰልፈኞቹ ከኖርዌይ ኦስሎ ነዋሪዎች ትኩረት እንደነበራቸው ለማወቅ ተችሏል።
በወገኖቻችን ላይ የደረሰውን ስቃይ በማስመልከት በኖርዌይ ኦስሎ ሰላማዊ ሰልፍ ተካሄደ
Filed in: Amharic