>

የሚሊዮኖች ድምፅ ለህሊና እስረኞች!

የሚሊዮኖች ድምፅ ለህሊና እስረኞች 1የሚሊዮኖች ድምፅ ለነፃነት አንዱ አካል የሆነው የህሊና እስረኞችን የሶሻል ሚዲያ ንቅናቄ ለአንድ ሳምንት የሚቆይ ዘመቻ ሲሆን ከሚቀጥለው ከእሁድ ከህዳር 14 እስከ 20/2007 የሚቀጥል ፕሮግራም ነው። በዚህ ዘመቻ ሚሊዮኖች የፖለቲካ ይሳተፋሉ፤ የፖለቲካ እስረኞች እንዲፈቱ፣ ተገቢ የሆነ አያያዝ እንዲኖራቸው፤ በሰላማዊ መንገድ የሚታሉትን ማሰርና ማዋከብ እንዲቆም ድምፃቸውን ያሰማሉ፤

ዘመቻው ለመንግስት ባለስልጣናት፣ ለመንግስት መስሪያቤቶች፣ ኤምባሲዎች፣ ለታዋቂ ግለሰቦች፣ ለአለም አቀፍ ሰብአዊ መብት ተሟጓች ተቋማት፣ ለተለያዩ ሚዲያዎች፣ በE‐mail በsms፣ በinbox ኢትዮጵያ ውስጥ ያለው የህሊና እስረኞች አያያዝና የእስር ሁኔታ፣ የታሳሪዎች ማንነትና አሁን የሚገኙበት ሁኔታ ወዘተ በመግለፅ በኢትዮጵያ መንግስት ላይ አዎንታዊ ተፅዕኖ እንዲያሳድሩ ማድረግ ነው።
በዚህ ዘመቻ የፖለቲካ አመለካከት፣ ቋንቋ ዘርና ሀይማኖት ሳይለየን ሁላችንም መሳተፍና ድምፃችንን ማሰማት ይኖርብናል። ሳምንቱን ሙሉ ሁሉም የህሊና እስረኞች የሚመለከት ቅስቀሳና ዘመቻ ሲኖር በተለየ ሁኔታ ደግሞ በየቀኑ የሚታወሱ የህሊና እስረኞች ይኖራሉ፤ እነርሱም የሚከተሉት ናቸው።
እሁድ፦ አንዷለም አራጌ፣ ናትናኤል መኮነን እና ሌሎች የአንድነት አባላት
ሰኛ፦ እስክንድር ነጋ እና ርዕዮት አለሙ
ማክሰኛ፦ አብርሃ ደስታ የሽዋስ አሰፋ እና ሀብታሙ አያሌው እና ዳንኤል ሽበሺ
ሮብ፦ በቀለ ገርባ፣ ኦልባና ሌሊሳና ሌሎች የኦሮሞ ታሳሪዎች
ሀሙስ፦ ተመስገን ደሳለኝ እና ውብሸት ታዬ
ዓርብ፦ የሞስሊም መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ እነአቡበከር
ቅዳሜ፦ ዞን ዘጠኝ
የሳምንቱ መሪ መፈክር የሚሊዮኖች ድምፅ ለህሊና እስረኞች!
Millions of voice for prisoners of conscience! የሚል ሲሆን በየቀኑ በተለየ ሁኔታ የሚቀነቀኑት መፈክሮች ደግሞ የሚከተሉት ናቸው
እሁድ ማክሰኞ እና ሮብ የሚኖሩት መሪ መፈክሮች፦

በሽብርተኝነት ሽፋን ሰላማዊ ታጋዮች ማሰር ይቁም
የህሊና እስረኞች እንጂ አሸባሪዎች አይደሉም
የሽብር አዋጁ ይሰረዝ
መንግስታዊ ሽበራ ይቁም
የዜጎች በሰላማዊ መንገድ የመደራጀት መብት ይከበር

ሰኞ እና ሀሙስ የሚኖሩት መሪ መፈክሮች፦

Because I am Journalist!
ጋዜጠኞች ማሰርና ማሳድድ ይቁም
ሀሳብን የመግለፅ ነፃነት ይከበር

ዓርብ ዕለት የሚኖሩ መሪ መፈክሮች፦

የኃይማኖት ነፃነት ይከበር
የሞስሊም መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ መሪዎች ይፈቱ
መንግስት በማህብረ ቁዱሳን ላይ እያሳደረ ያለውን ተፅዕኖ ያቁም
መንግስት በኃይማኖት ጉዳይ ላይ ጣልቃ አይገባም የሚለው የህገ መንግስቱ ድንጋጌ ይከበር

ቅዳሜ ዕለት የሚኖሩ መሪ መፈክሮች፦

ሰብአዊ መብት በኢትዮጵያ ይከበር
Blogging Is Not A Crime
ሀሳበን የመግለፅ መብት ይከበር
እንደአስፈላጊነቱ ሌሎችም መፈክሮች ይኖራሉ።

Filed in: Amharic