>

ዛሬ አገራችን እጅግ ውስብስብ በሆኑ ችግሮች ተተብትባ የምትማቅቅበት ጊዜ ነው...!!! (ወ/ሮ መሶበወርቅ ቅጣው፤ በባልደራስ የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት ዕጩ ተወዳዳሪ)

ዛሬ አገራችን እጅግ ውስብስብ በሆኑ ችግሮች ተተብትባ የምትማቅቅበት ጊዜ ነው…!!!
ወ/ሮ መሶበወርቅ ቅጣው፤ በባልደራስ የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት ዕጩ ተወዳዳሪ
 
መንግሥት ሊታደጋቸው አልቻለም !! “

” ዜጎች በማንነታቸውና በሀይማኖታቸው ምክንያት በገጀራ ሲቆራረጡ፣ በቢላዋ ሲታረዱ፣ ሆዳቸው በስለት እየተሰነጠቀ ጽንሶች በሜዳ ላይ ሲጣሉ፣ አስከሬኖች እንደአልባሌ እቃ እየተወረወሩ በአንድ ጉድጓድ ሲቀበሩ፣ ንብረቶቻቸው ሲዘረፉ፣ ቤቶቻቸው በእሳት ሲጋዩ፣ ቤተ እምነቶቻቸው ሲቃጠሉ እና ሌሎችም ከፍተኛ ሰቆቆ ሲፈፀምባቸው ሰላማቸውን የመጠበቅና መብታቸውን የማስከበር ግዴታ ያለበት በሥልጣን ላይ ያለው መንግሥት ሊታደጋቸው አልቻለም፡፡ አዲስ አበባ ላይም ‹‹ከአዲስ አበባ ልዩ ጥቅም ይገባናል›› ከማለት አልፈው ‹‹በአዲስ አበባ የባለቤትነት መብት አለን›› በማለት ከፍተኛ በደል እያደረሱ ይገኛሉ፡፡”
ወ/ሮ መሶበወርቅ ቅጣው፤ በባልደራስ የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት ዕጩ ተወዳዳሪ ! ወረዳ/ ምርጫ ክልል 12/13
Filed in: Amharic