>
5:13 pm - Thursday April 19, 6131

መንግሥት በአማራ ላይ የጀመረውን የዘር ማጥፋት እንቅስቃሴ ያቁም...!!!  ባልደራስ 

መንግሥት በአማራ ላይ የጀመረውን የዘር ማጥፋት እንቅስቃሴ ያቁም…!!!

 ባልደራስ 

በኦሮሚያ፤ ሆሮጉድሩ ወለጋ አቤ ደንጎሮ አማራዎች ካለፈው ቅዳሜ የካቲት 27 ቀን 2013 ዓ.ም. ጀምሮ እንደ አዲስ በነሲብ እየተገደሉ ነው። የሚገደሉትም በመንግሥታዊ የእዝ መዋቅር በታገዘ ታጣቂ ቡድን ነው። ከግድያ የተረፉት ታግተው ወደ ጫካ ተወስደዋል። ሕፃናት እየታነቁ ወንዝ ውስጥ መወርወራቸውንም ከአካባቢው የወጡ ዘገባዎች ያሳያሉ። በጉጂ፤ አማሮ ተመሳሳይ ብሔር ተኮር ጥቃቶች እየተፈፀሙ ነው።
በመሆኑም ባልደራስ ለእውነተኛ ዴሞክራሲ ፓርቲ (ባልደራስ) በንፁሃን ላይ በደረሰው ግድያ የተሰማውን ሀዘን እየገለፀ መንግሥት በአማራ ላይ የጀመረውን የዘር ማጥፋት እንቅስቃሴ እንዲያቆም ያሳስባል። ከግድያ የተረፉትን ወደ ቀደመ ሰላማዊ ኑሯቸው እንዲመልስ እንጠይቃለን።
በተመሳሳይ በየመን፤ ሰንዓ ከተማ ጥቂት የማይባሉ ኢትዮጵያዊያን በሚገኙበት የስደተኞች መጠለያ ላይ የእሳት ቃጠሎ ደርሶ በርካቶች ሙተዋል። ባልደራስ ለቤተሰቦቻቸው እና ለመላው ኢትዮጵያውያን መፅናናትን ይመኛል። ፈጣሪ የሟቾችን ነፍስ ይማር!
Filed in: Amharic