>
5:13 pm - Saturday April 20, 7320

ዩኒቨርሲቲዎቻችን የተማሩ ወጣቶችን በማፍራት ፈንታ ዱላና ድንጋይ የሚያነሱ ወጣቶችን ካመረቱ ችግር አለ ማለት ነው. . .(ታማኝ በየነ)

ዩኒቨርሲቲዎቻችን የተማሩ ወጣቶችን በማፍራት ፈንታ ዱላና ድንጋይ የሚያነሱ ወጣቶችን ካመረቱ ችግር አለ ማለት ነው. . . 

 ታማኝ በየነ

“… ሰው ያስባል ፤ የተነገረውን ሁሉ ይዘን እንደ ጎርፍ ወደየአቅጣጫው እንሄዳል? ወይንስ ቆይ ለምን እንዴት? መቼ ብለን እንመረምራለን?  ይሄንን ማሳየት ከቻላችሁ ነው የተመረቃችሁ የምትባሉት፡፡ አለዛ በሀገራችን ውስጥ ያለው አደጋ በጅምላ  መነዳት ነው፤ ማሰብ መቻል አለብን ፤ የተወለድንበትን “ብሔር ብሄረሰብ” የሚባለውን ነገር ማንም በጉልበት አይነጥቀንም ፤ ከኛው ጋር የሚኖር ነው ግን ይሄ የመለያየት ምክንያት ሆኖ በየጊዜው ዩኒቨርሲቲዎች የተማሩ ወጣቶችን ማፍራት ቀርቶ በየጊዜው የሚደባደቡ ካወጣ ችግር አለ! ለዘመናት ለአፍሪካ አርዓያ የነበረች ሀገር በዚህ መልክ በየአቅጣጫው የሞት መርዶ በየቀኑ ምንሰማበት ከሆነ አገር ከሆነ ራሳችንን ነው መጠየቅ ያለብን፡፡ በኢትዮጵያ ውስጥ 1 ዩኒቨርሲቲ  ብቻ ነው የነበረው ዛሬ ብዙ ዩኒቨርሲቲ አለ የዛ ሁሉ ዩኒቨርሲቲ ወጣት የምርምር ብቃት ፣ የት ደርሶ ነው? አንዱ ብሔር ካንዱ በየምክንያቱ የሚደባደበው?   በየምክንያቱ የሚጣላው?  ራሳችንን እንጠይቅ ! እኔ ከውጭ ነው የመጣሁት እኔና መንግስት እንዳማንስማማ ታውቃላችሁ  … እና እዚ ጋ ስታዩኝ ይሄ ሰውዬ ብልጽግና ነው ብላችሁ እንዳይሆን .. እመረምራለሁ እጠይቃለሁ … የሚሰማኝን እንደዜጋ እቃወማለሁ፡፡ በጎ ሲሆን ደግሞ በጎ ነው እላለሁ!  በልዩነት መኖር እንደሚቻል ማሳየት መቻል አለብን ፡፡
በፖለቲካ እሳቤያችን እኔና መንግስት አንስማማም ግን በውስጡ ያሉ ዜጎች ደግሞ ሁላችንም እኩልነን በዜግነት፡፡ የዜጎች ሞት፣ የዜጎች መጎዳት እያንዳንዳችንን ሊያመን ይገባል፡፡ ዛሬ በዚች ሰዓት ያለምንም ጥፋታቸው የሚራቡ ፣ ሜዳ ላይ የወደቁ ዜጎችን ማሰብ መቻል አለብን ፡፡ ከኛ ደስታ ጎን ብዙ መከራ በኢትዮጵያ ውስጥ አለ፡፡ ይሄን የመቀየር ደግሞ የዕናንተ የወጣቶች ፣ የተማራችሁት ኃላፊነት ነው፡፡ መንስትን በድንጋይ ሳይሆን በሀሳብ በመሞገት ወገቡን አንቀን መያዝ አለብን፡፡ እኛ የምንለውን ነው ማድረግ ያለበት፡፡ ማለት ህዝብ የሚፈልገውን፡፡ ይሄን የምናገረው በመንግስት መሪዎች ፊት ነው፡፡ [] ያለዚያ ህዝብ ሲያምጽ ከየትም ጉድጓድ ውስጥ አውቶ ለፍርድ ያቀርባል፡፡ ይሄ ከመምጣቱ በፊት ህዝብ የሚፈልገው በማድረግ ኢትዮጵያ ሰፊናት በቂነች ያጣነው በቂ ሰፊ አዕምሮ ያለው ፖለቲከኛ ነው ያጣነው፡፡ ስለዚህ አደራ የምላችሁ ለፍተው ጥረው አሳድገዋችሁ በዓልምዓቀፍ መድረክ ኢትዮጵያን የምትዎክሉ ዜጎች እንጅ በሰፈር የምተደባደቡ እንዳልሆናችሁ አርዓያ ሁናችሁ እንድታሳዩ በአክብሮት እጠይቃለሁ፡፡ በዚህ መንፈስ ከተንቀሳቀስን የኢትዮጵያ እድል ሰፊ ነው ፣ ብሩህ ነው ፣  ግን የመንግስት ብቻ ሳይሆን የእያንዳንዳችን ኃላፊነት ነው፡፡ በኢትዮጵያ ውስጥ ሰላም፣ መከባበር፣ አንድነት እንዲመጣ በጋራ እንስራ ! ጠይቁ ! መርምሩ! የሙህራን ዋናው መለኪያ ይሄነውና በፍጹም ለኢትዮጵያ ሰላም፣ ለእኩልነት ፣ በኢትዮጵያዊነት በአንድነት ለመኖር የሁላችንን ድርሻ ይጠይቃልና በርቱ! እንኳን ደስ አላችሁ! እግዚአብሄር ይስጥልኝ፡፡”
ጥር 2013 ዓ/ም ኢትዮጵያ
Filed in: Amharic