>

"መተከል ሁለተኛው ማይካድራ ነው!!! (አምሀራ ኢንፎርመር)

መተከል ሁለተኛው ማይካድራ ነው!!!

አምሀራ ኢንፎርመር

 

* መተከል እና አሳዛኝ ውሎዋ!!
* ሰባት ቤተሰብ ከአንድ ቤት ታርደው ተጥለዋል
*”… ጉምዞቹ አፈሩን እያነሱ እየው ይህን አፈር አሽትተው የጉምዝ መሬት እኮ ነው!” ይሉናል
 
መተከል ዞን ድባጢ ወረዳ በዛሬው ቀን የሳስማንደን  ቀበሌ ህዝብ ሃብቱን ንብረቱን ቤቱን ያፈራውን አዘመራ ጥሎ መውጣቱ ታውቋል። ወጣቶች  አሮጊቶችንና አቅመ ደካሞችን በመሸከምና በማገዝ ከሞት ቀጠናው እንዲወጡ አድርገዋል።
የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ረዕሰ መስተዳደር አቶ አሻድሊ ሀሰን አቶ ጌታሁንና አቶ አትንኩት ሽቱ የተባሉ ግለሰቦች ጠቅላይ ሚኒስትሩን ጨምሮ ከፌደራል የሚመጡ አካላትን  አሉ በማባሉ ምክንያት እውነተኛውን የህዝብ ጭፍጨፋ፣ ማፈናቀልና   ዘረፋ ለማድበስበስ ላይ ታች ሲራወጡ ውለዋል።  ከፌደራል መንግስት ወደ ቦታው የሚጓዙ አካላት በሚገኙበት የህዝብ መደረክ ላይ #የመተከል_ህዝብ እንዳይሳተፍ ለማድረግ ከፍተኛ ተልዕኮ ወስደው ሲሰሩ እንደዋሉ አረጋግጠናል። ሴረኞቹ በማያዋጣውና ለችግሩ መፍትሔ በማያመጣው ሴራቸው በገንዘብ ሳይቀር የገዟቸውን አፈ ቀላጤ ጉምዞችን ሲያሰለጥኑ አቅጣጫ ሲሰጡ ውለዋል። በዚህ ሴራቸውም ከገዳይ ወገን የሆኑትን ጉምዞችን ተፈናቅለዋል ብለው ጉዳዩን ለማድበስበስ ከጃዊና ከተለያዩ አካባቢዎች እያጓጓዙ ግልገል በለስ ከተማ ቻይና ካምፕ አካባቢ አስፍረዋቸዋል።
 ከመተከል ዞን ድባጢ ወረዳ ሳስ ማደልና ፋርዘይት ቀበሌዎች አማራው ሙሉ ለሙሉ መፈናቀሉን መዘገባችን ይታወሳል።
ከቦታው በደረሰን መረጃ መሰረት የተፈናቀሉ አማራዎች እስከአሁን ድረስ በ13 ተሽከርካሪዎች መንታውሃ ደርሰዋል። ተሽከርካሪ ያላገኙት ደግሞ አሁንም ከፋርዘይት ወደ ድባጢ በእግራቸው ከድባጢ ደግሞ ወደ መንታውሃ በመኪና እየመጡ እንደሆነ አረጋግጠናል።

https://www.facebook.com/Amharainformer/videos/778175692907668/

Filed in: Amharic