>

ጋይስ….. አገራችን እንዳትፈርስ...!!! (አሳዬ ደርቤ)

                ጋይስ….. አገራችን እንዳትፈርስ…!!!

አሳዬ ደርቤ

ከንቲባው ዘርፎ አይከሰስ- ሽመልስ ዘልፎ አይወቀስ

ድሆች በቆጠቡት ብር- የካድሬ ጎጆ ይቀለስ

ታከለ ወረደ ስንል- ታከለች በቦታው ትንገስ

ሸገር ቤቷን ተነጥቃ- በሰላም ዳቦዋን ትጉረስ

.

ጋይስ…. አገራችን እንዳትፈርስ

ለትምህርት የሄዱ ሴቶች- ጫካ ውስጥ ቀልጠው ይቅሩ

የዘር ጭፍጨፋ ፈጽመው- ‹‹ግጭት›› በማለት ይጥሩ

ኀዘን፣ ንዴታቸውን- አንገት በማረድ ይግለጹ

ቤታችንን በማቃጠል- ንብረት በማውደም ይመጹ

.

ጋይስ…. አገራችን እንዳትፈርስ

የመኮነን ሐውልት ይንኮት- እንዳሻቸው ያፈናቅሉ

ኦሮሞ በያዘው ወንበር- አማራን ዳውን ይበሉ

መሬቱንም ሰማዩንም- በጎጥ ቀላድ ይካፈሉ

ጃዋር የታሰረ እለት- አጃቢው ሆነን እንታሰር

ፖሊስ የከበበው ቀን- ሟቾች ሆነን እንቀበር

የነፍጠኛውን ሥርዓት እናውግዝ- የገዳ ሥርዓት እንማር

ልማት ይጥፋ- ምርጫው ይቅር

.

ጋይስ- አገራችን እንዳትፈርስ

ሲመቷችሁ አታልቅሱ- ሲቀሟችሁ አትክሰሱ

ዝም ብላችሁ ቀበሮ ጋር- ከዐቢይ ፓርክ ተናፈሱ፡፡

Filed in: Amharic