>

አቶ ሽመልስ አብዲሣ ዛሬ የሃጫሉ ቀብር ሥነስርአት አምቦ እየተካሄደ ባለበት ወቅት በOBN ያደረገው ንግግር  አቤል ብርሀኑ

አቶ አብዲሣ ዛሬ የሃጫሉ ቀብር ሥነስርአት አምቦ እየተካሄደ ባለበት ወቅት በOBN ያደረገው ንግግር 
አቤል ብርሀኑ

* ሃጫሉ “አንድ ቀን ይገድሉኛል እንዳለ አለፈ”
ሃጫሉን አንዴ ሳይሆን ሶስት ጊዜ ነው የገደሉት
 
ሃጫሉን አንድ ግዜ ብቻ አይደለም የገደሉት አስከሬኑ ወደቤተሰቦቹ እየተሸኘ ሳለ መሣሪያ የታጠቁ አስከሬኑን ነጥቀው ወደ አዲስ አበባ መለሱት ፣ ህዝብ በተኩስ ለውጥ እንዳይጎዳ ብለን ዝም አልናቸው ፣ ይህም አንሶ የብልፅግና ፅ/ቤት ድረስ ዘልቀው ሥራ ላይ የነበረውን ሰው በመግደል ግጭት ለመቀስቀስ ሞከሩ፣ ያንንም በትዕግሥት አለፍነው ፣ በትናንትናው እለት ደግሞ ኦነግ ሸኔና የወያኔ ታጣቂዎች በቅንጅት ወላጆቹ ቤት ድረስ ዘምተው አጎቱን በጭካኔ ገደሉት፣ ይህ ለሃጫሉ 3ኛ ሞት ነው ።
 
ለሃጫሉ ግድያ ተጠየቂዎቹ ኦነግ ሸኔ ወያኔና በህዝብ ትግል ገብተው እዚህ አዲስ አበባ ቁጭ ብለው ህዝብ የሚያምሱ ናቸው ፣ ሃጫሉን ለእርድ ያዘጋጁት የግዲያው ተባባሪዎች ከሳምንት በፊት ሚዲያቸው ላይ አቅርበውት ምን እንደጠየቁት ማንም ሰው የሚያውቀው ነው፣ ያ ቃለመጠይቅ የተዘጋጀው ለሴራቸው ስኬት ህዝብን ከህዝብ ለማባላት በማሰብ እንደነበር ግልጽ ሆኖአል። ከጥያቄያቸው አንዱ ትግራይ ሂዶ ከወያኔ ጋር መነጋገር እንዴት ወንጀል ነው ትላለህ ? ድሮ ድሮ ኦሮሞ ኦሮሞ ትል ነበር አሁን ቋንቋህን ቀይረሃልም ነበር ያሉት ። 
 
ሃጫሉ እነርሱ የግል ህይወታቸውን ሲያደላድሉ ከጠላት ጋር ግንባሩን ሰጥቶ ስተናነቅ የኖረና ጨቋኝ ሥርአት ለማንኮታኮት መስዋእት የከፈለ ጀግና ነው ፣ በነፃነት ወደ አገራቸው ሲመለሱ አክብረን የተቀበልናቸው ግን ለህልፈቱ ተባባሪ ሆኑ ። 
ከአሁን ቦሃላ ትዕግሥታችን ተሟጦአል። ያሳየነው ትእግሥትና ፍቅር ከፍርሃት የመነጨ አይደለም። ወያኔ፣ ኦነግ ሸኔና አዲስ አበባ ሆኖ ውጥረት የሚያመርተው ቡድንና ከግብፅ ጋር ተባብረው አገራችንን እንዲያተራምሱ የሚፈልጉ ሃይሎች አላማቸው አይሳካላቸውም ፣ ክልላችን ሰላም እየነሱ ያሉ እነዚህን ሃይሎች የገቡበት ገብተን ከክልላችንን እናጠራቸዋለን። 
 
ከበሰበሰው ሥልጣን ጠራርገን ያባረርነው ወንጀለኞች እርስ በርስ አባልተውን ዳግም ወደሥልጣን ሊመለስ አይችልም ። ኦሮሞ ግንድ ነው፣ አባት ነው ፣ታላቅ ነው በኖረው ባህልህ ከሁሉም ህዝብ ጋር በፍቅር መኖርህን ቀጥልበት። እርስ በርስ በመባላት ለጠላቶቻችን ሴራ እንዳንመች አደራ እላለሁ ……”
Filed in: Amharic