>
5:13 pm - Saturday April 18, 0207

የታላቅ ምክር ፤ ለጠሚ ዐቢይ አሕመድ ...!!!  ዘመድኩን በቀለ 

የታላቅ ምክር ፤ ለጠሚ ዐቢይ አሕመድ …!!!

ዘመድኩን በቀለ 

በባሌም በቦሌም ቢሆንም በኢሜይልም በፋክስም በነፋስም ብቻ መልእክቴን አድርሱልኝ!!
 
ከራየን ወንዝ ማዶ የተጻፈ። 
•••
ኦቦሌሶ፥ ክቡር ሆይ !! በመወለድ እኔ ዘመዴ በሁለት ዓመትም ቢሆን እበልጥሃለሁ። በሌላ አነጋገር ታላቅህ ነኝ ማለት ነው። አንተ አሁን እንደ ዕድል ሆኖ ይህቺ ታላቅ ሃገር በእጅህ መዳፍ ላይ ወድቃለች። በ21ኛው መቶ ክፍለ ዘመን የሀገሬ የኢትዮጵያ መሪዋም የእኔም ጠቅላይ ሚንስትሬም እንድትሆን ታሪክም ፈጣሪም ተባብረው ሹመውሃል። እናም ወንድም ዓለም መወቃቀሱ ለነገ ይደር ይቆየንና ለዛሬ ግን ይህቺን የ3ሺ ዘመን ሥርዓተ መንግሥት ያላት ሀገርን ለምትመራ ለአንተ የልቤን ልመክርህ ነኝና ስማኝ። መልእክቴ እንዴት እንደሚደርስህ ባላውቅም ከደረሰህ ግን በፈጠረህ ስማኝ። በኢየሱስ ስም። በጌታህ ስም ይሁንብህ ስማኝማ። በአባትህ አምላክ በአላህ ይዤሃለሁ ስማኝማ
አንደኛ
ኦቦሌሶ አሁን ሳትወድ በግድህ አደገኛውን አውሬ ለዘመናት ፍየል በጎቻችንን ሲፈጅ ሲያስፈጅ የኖረውን የነብሩን ጭራ ይዘኸዋል። አደራህን እንዲች ብለህ እንዳትለቀው። እንዲች ብለህ አልኩህ። አባ ገዳ፣ አባ ኮዳ፣ ያገር ሽማግሌ፣ የመንደር ኮልኮሌ ቄስም ሼህም ነኝ ብለው ተሰልፈው እንሸምግል ብለው ቢመጡ እንዳትሰማቸው። እርምጃህ ከምር ከሆነ ዓለሙ ሁሉ ከአንተ ጋር ይቆማልና አሁን ማንንም እንዳትሰማ። እንዳትሰማ ያስበሉሃል። አቢቹ ነብሩን ከለቀቅከው እንክትክት አድርጎ አንተኑ ከነዘር ማንዘርህ ነው የሚፈጅህ። እመነኝ ያጠፋሃል። ሰምተሃል !! ነግሬሃለሁም።
ሁለተኛ
የአደገኛውን ነብር ጉዳይ መላ ካበጀህለት በቀጥታ ሳትውል ሳታድር ዕለቱኑ ገስግሰህ ቆፍጠን ብለህ እንደራስ መኮንን ትግራይ መቀሌ ግባ። የነብሩ ጓደኞች የቀበሮዎቹ መሸሸጊያ ጉድጓድ ወደሆነችው መቀሌ ገስስግስ። ከጥቃቅኖቹ ቀበሮዎች ጀምረህ እስከ አሮጌ ቀበሮዎቹ ድረስ እያንዳዳቸውን ለቃቅመህ ጎትተህ ወደ ለይቶ ማቆያ አስገባቸው። የወይኗን የኢትዮጵያን ቅጥር ሾልከው እየገቡ የሚያተራምሱ ቀበሮዎችን አጥምደህ ያዛቸው። መቀሌ ሂድ። ሂድ መቀሌ። ህዝቡም ያግዝሃል ሂድ።
•••
መቀሌ ገብተህም በመጀመርታ ሰካራሙንና አውርቶ አደሩን ከመለስ ዜናዊ ሞት በኋላ ምላስ ለሌላቸው ጎልዳፋ፣ ተብታባ የህወሓት ጅጁ ሽማግሌዎች አፈቀላጤ በመሆን ለሆዱ ሲል ትግሬነኝ ብሎ የትግራይን ህዝብ ከቀሪው ከኢትዮጵያ ህዝብ ጋር የሚያፋጀውን ሆድ እንጂ ጭንቅላት አላባ ባንዳውን፣  “ጦርነቱን ከመሃል ሃገር ከአዲስ አበባ ነው የምንጀምረው” ብሎ በአደባባይ በግልፅ ህወሓት ድርጅቱ ምን ማድረግ እንደምትፈልግ የለፈለፈውንና ሃጫሉን በማስገደል ሀገር በአፍጢሟ እንድትቆም ሥራ የጀመረውን “ የወሎ ራያ ተወላጁንና ሆዳም ዐማራ በትግሬ ካባ የተሸፈነውን ትግርኛ በቅጡ መናገር ሳይችል ትግሬ ነኝ ብሎ ለሆዱ ያደረውን ሆዳሙን፣ ሰካራሙን፣ ሦስት ሴት በአንድ ሌሊት አቅፎ የሚያድረውን ዘማዊ አይተ ጌታቸው ረዳን ማንቁርቱን አንቀህ አንጠልጥለህ ለፍርድ አቅርብ።
ሦስተኛ
ድሮ ድሮ የህወሓት ተቃዋሚ መስሎ ነፃ ጋዜጠኛ ነኝ ሲል የከረመውን፣ ከቅንጅቶች ጋር በመታየት ከዚያም ግንቦት ሰባት ነኝ ሲል የከረመውንና ሁሉ አልሳካለት ሲል ጠጠው ብሎ ሀገሩ መቀሌ ገብቶ የህወሓት ካድሬ የሆነውን በቀድመ ጊዜ ከሶማሊው አብዲኢሌ ጋር ሆኖ ህዝብ ሲያፈጅ የነበረውን አሁን ደግሞ የጃዋር ገረድ የወንድ እጅ ጠብቆ አዳሪውንና “እንወራረድ” ብሎ ተወራርዶ እንደተናገረው ሃጫሉ እንደሚገደል አስቀድሞ በገደምዳሜ ነግሮ በውርርዱ መሰረት እንደተናገረው አዲስ አጀንዳ ፈጥሮ ሀገር እንድትታመስ ያደረገውን፣ ለብዙ ዐማሮች መገደል፣ አሁንም መገደል፣ ለቅርስ መውደም መንስኤ የሆነውን ሆድ አደር እንኩቶ የጋዜጠኛ ቅራሪ ባሻጋታ ጭንቅላቱን የዓድዋ ተወላጁን ዳዊት ከበደን ካለበት ሥፍራ በሀገሪቱ ሕግ መሠረት ጠፍረህ፣ ጠፍንገህ አንጠልጥለህ ወደ ማዕከላዊው መንግሥት በማምጣት ለፍርድ አቅርበው።
•••
ልክ ዐማራ ገብተህ፣ በኦሮሚያ፣ በሶማሊያ፣ በአፋር፣ በቤኒሻንጉል፣ በደቡብ፣ በሐረሬ፣ ገብተህ ከተራ እስከ ከፍተኛ ወንጀለኞች እንደምትይዘው ሁሉ ትግራይም ግባ። ግባና ተጠርጣሪ ወንጀለኞችን በሙሉ በሃገሪቱ ሕግ መሠረት ለሚናገሩት፣ ለሚቀሰቅሱት የወንጀል ተግባር ተጠያቂ አድርጋቸው። ሂድ፣ ጨክን። ያን ያደረግክ ጊዜ መንግሥትህ ለጊዜውም ቢሆን ትጸናለች። ወላዲተ አምላክ ምስክሬ ናት። አበደን እውነቴን ነው። ይህን አድርግ። ስታየው ቀላል ይመስላል። ነገር ግን ውጠቱ እጅግ ከባድ ነው። ደግሞስ ያስነጠሱ ዜጎች ሁሉ ሲታሰሩ የሚያስታውኩ የህወሓት ሰዎች የማይያዙት ከምንድነው። በአንድ ሀገር ሁለት ዜግነት የለም።
•••
ትግራይ በኢትዮጵያ ግዛት ውስጥ ያለች ክፈለ ሃገር ናት። አንተ ደግሞ የትግራይም ጠቅላይ ሚንስትርዋ ነህ። ወያኔ የተተፋ፣ የተናቀ፣ እግዚአብሔር ያዋረደው ኃይል ነው። እናም ይህን ነውረኛ የግብፅ ቅጥረኛ ኃይል ማስተንፈስ ግድ ይልሃል። አንተ ደግሞ የጠረጠርከውን ወንጀለኛ በሙሉ ካለበት ሄደህ ለሕግ የማቅረብ መብቱ አለህ። አልታዘዝ ያለ ካለ ዠልጠው። በእውነት ይሄን ያደረግክ ጊዜ የህወሓት አዚሟ ይሰበራል። የሱዳኑ መተቷም ይከሽፋል። በቀጣይ ጌታቸው አሰፋንም፣ ስብሃት ነጋንም፣ ስዩም መስፍንንም አንጠልጥለህ ለፍርድ ለማቅረብ ጉልበትም ይሆነሃል። Do It !!
•••
የእኔ ዛፍ ቆራጭ ስማኝማ። የዐቢይ መንግሥት እኮ ዐማራ፣ ሱማሌና ኦሮሞ ላይ ብቻ ነው የሚበረታው ለሚሉህም ሰዎች አቅምህን አሳያቸው። አቢቹ ህወሓትን ይፈራታል የሚለውንም የህዝብህን ስጋትና ሀሜት በቶሎ አስወግድ። ሃገሪቱ እንድትረጋጋም ከፈለክ ዛሬ ነገ ሳትል ትግራይ ገብተህ ወንጀለኛን፣ ተጠርጣሪን ለፍርድ አቅርብ። ዛፉን መልምለህ መልምለህ አሁን የቀረህ መቀሌ የቀረው የበሰበሰ፣ ያረጀ ቅጥል ፍሬ አልባው ግንድ ብቻ ነው። ትል የበላው፣ የሻገተ ግንድ። ከነሥሩ ነቅለህ ለትግራይም፣ ለኢትዮጵያም እረፍትን ስጥ። Do It ብዬሃለሁ Do It በእንግልጣር አፍ ነግሬሃለሁ።
አራተኛ
እንደሚባለው ኦቦ ለማ መገርሳም ቢሆን ከአንተ ጋር ካልሆነ፣ ከኢትዮጵያም ጋር ካልሆነና እንደሚባለው ውሎ አዳሩ ከእነ ሀረግሬሳ ጀዋር ጋር ከሆነ በኦሮሚያ ክልል ሕግ ለማስከበር በብርቱ ትቸገራለህ። የፌደራሉ ፖሊስና የመከላከያ ሠራዊቱ ከወጠጤው ነውጠኛ ሰርቆ አደር ሰነፉ ቄሮ ተብዬ ቆርቆሮ ጋር ብቻ ሳይሆን ከኦሮሚያ ፖሊስም ዘንድ መጠነኛ ችግር ይገጥመዋል። አንዳንድ ቦታም እየታየ ያለው እሱ ነገር ነው። እናም ኦቦ ለማ ከአንተ ጋር ካልሆነ የሆነ ቀን ለምሳ ሊያስብህ ይችላልና አንተ ቀድመህ ቁርስ ላይ አወራርደው። አጣጥመው። ኢትዮጵያ ፊት የቆመ እንቅፋት ከሆነ ጨከን ብለህ አሳርፈው። ገለል አድርገው። ጡረታውን አስከብረህ ጡረው።
•••
አንተ ግን ጸሎቱ ላይ በርታ። ሰባክህን ግን ለጊዜው አቁመህ ወታደር ሁን። እንደ ወንድ ሁን። ወንድ ወንድ ሽተት። ወንድ ምሰል። ቱታህን አውልቀህ ቀበቶ ያለው ሱሪ አጥልቅ። እንደ ሴት ስትኳኳል አትዋል። ፌር ለወንድልጅ ምን ይሠራለታል። መንጌን ተመልከት። ጥቁር ነው ግን ወንድ ነበር። ጀርመን አሜሪካ፣ ፈረንሳይም ኢትዮጵያም ሀገር የሆኑበትን መንገድ ተከተል። ይሄን ጌታ ያውቅልኛል ብለህ ቸል ብለህ ካየኸው እመነኝ ቀጣዩ ተረኛው ሟች አንተ ነህ። ነፍሰ ገዳዮቹ የክልል ፕሬዘዳንት ገድለዋል አስገድለዋል፣ የወረዳና የዞን፣ ተራ የመንግሥት ሠራተኛ ሳይቀር ገድለው አሳይተውሃል። መቀሌ
ተቀምጠው ጀነራል ሰዓረን ክዶናል ብለው አስወርተው ሲያበቁ ገድለውታል። የሰዓረ ሚስት ብትገረፍ ገዳዮቹን ትነግርህ ነበር። ራሷንም መጠርጠሩ ብልህነት ነው። እሷ ትግሬ ሰዓረ ዐማራ ነው። ምንአልባትም የድርጅቷን ተልእኮ ሳትወጣ አትቀርም የሚሉ አሉ። እና አሁን አርቲስት ሃጫሉንም ከድቶናል ብለው እነ ጃዋር እንዳስገደሉት እውነት ነው። መሪው ወንድሜ ሰዎቹ ነፍሰ ገሳዮች ናቸውና ይገድሉሃል። ሳይቀድሙህ ቅደማቸው። ሰበካህን አቁም። ይሄን ሁሉ ምክር መክረንህ አልሰማ ብለህ መከራ በላይህ ላይ ቢመጣ የራስህ ጉዳይ ነው።
• ሰኔ 16/2010 ዓም ከቦንብ ድንሃል።
• ሰኔ 15/2011 የክልል ፕሬዘዳንትና ጄነራሎችን አጥተናል።
• ዘንድሮም ሰኔ22/2012 ዓም ታዳጊውን ሃጫሉን ኣሳስተው ገድለውታል።
አልሰማ ካልክ የሚቀጥለው ዓመት ሰኔ ከደረስክ የአንተን ነፍስ ይነጥቁሃል። የቀረሃቸው አንተው ብቻ ነህ። ሰምተሃል። ወያኔ ህወሓት፣ ግብጽ፣ የወደቀው የአልበሽር የሱዳኑ ርዝራዥ፣ ጃዋርና ኦነግ ሸኔ የበቀለ ገርባው ኦፌኮም አንድ ላይ ነው የሚሠሩት። ተመልከት የፀጋዬ አራርሳ ፌስቡክ ሲዘጋበት በቀጥታ የተቀበሉት የህወሓቶቹ እነ አሉላ ሰሎሞን ናቸው። ይሄ ማለት እንዴት እንደሚናበቡ ማየቱ በቂ ነው። በዚህ ላይ እውነት ሆኖ በእንቅርት ላይ ጆሮ ገድፍ እንዲሉ ለማ መገርሳ ከጠላት ጋር ካበረ አለቀልህ።
አምስተኛ
ብትዘገይም የሀረግሬሳዋን የOMN ን ባለቤት ሸቤ አስገብተህ በመዝጋትህ ደግ አደረግህ። የሀገሪቱን ስልክና ኔትወርክ ኢንተርኔትም በመዝጋትህ አበጀህ። ቀድመህ ባለማድረግህ አሁን የደረሰው አደጋ ቢደርስም አሁንም ጥሩ ጊዜ ነው። ቢረፍድም ከመቅረት ይሻላል። አሁን ደግሞ የሚቀርህን ልጠቁምህ። በፍጥነት ዛሬ ነገ ሳትል የወያኔ ህወሓት ምላስ የሆኑትንና ትግራይ መቀሌ መሽገው ያሉትን ሚድያዎች በሙሉ ልሣናቸውን ዝጋው። ከሱሉልታ ሳታላይት ከባልቦላው ጠርቅምባቸው። ይሄን ያደረግክ ጊዜ ምላሳቸውን እንደቆረጥከው ቁጠረው። የፌደራል መንግሥቱን ኤቴቪንና የኢትዮጵያ ራዲዮን ብቻ ይከታተሉ ዘንድም ፍረድላቸው። ህዝቡ ምንም አይልም። አትፍራ ነግሬሃላሁ።
ስድስተኛ
ጦምም ቢሆን እንደር እንጂ ከየትም እንደየትም ብለህ የሀገሪቱን የብር ኖት ነገ ዛሬ ሳትል ቀይረው። 27 ዓመት ሙሉ የተዘረፈ ብር መቀሌ ነው በኮንቴይነር ተቀምጦ ያለው። ይሄን ሥራ አጥ የኦሮሞ ወጣት የሚገዙት በእሱ ብር ነው። ቻይና ሳይቀር ብር እያሳተሙ በኮንቴይነር ሸክፈው እንደ አስቤዛ ያስገቡ የነበሩ ጉደኞች እኮ ናቸው። እና ይሄን የጥፋት ምንጭ ለማድረቅ ወሳኙ ነገር ብሩን አሁኑኑ ቀይር። ከዚያ ለውጡን ታየዋለህ። ያኔ አንድ የትግራይ ገበሬ ከመሬት ተነስቶ 10 ሚልየን ብር ባንክ ሊቀይር ከመጣ የምትጠይቀውን ጥያቄ ትጠይቀዋለህ። በእናትህ። በዝናሽ በምትወዳት ሚስትህና ልጆችህ ልለምንህ ይሄን ነገር አፍጥነው። Do It  !!
•••
አሁን እንኳ ዶላርና ዩሮ ከ45 ብር በላይ በጥቁር ገበያ የሚዘረዝሩት እኮ እነሱ ናቸው። ገና ለገና ብር ሊቀየር ይችላል በማለት በኮንቴነር ያሸጉትን ብር ወደ ዶላርና ዩሮ እየቀየሩት እንደሆነ እያየን፣ እየሰማንም ነው። ፈጥነህ በዋሻ በመጋዘን ያስቀመጡትን ብር አንድደው ይሞቁት ዘንድ ቀይረው። ወረቀት አድርገው። ሰምተሃል።
•••
ቢወዱህም ቢጠሉህም። ብንወድህም ብንጠላህም፣ ቅር የምታሰኘን ቢሆንም ስለ ብዙ ነገር ሲባል አሁን ከአንተ ሌላ ምንም ምርጫም አማራጭም የለንም። ይሄንን በደንብ እወቅ። ደግሞም ታውቀዋለህም። አሁን ሚልዮኖችም ከአንተ ጋር ናቸው። ይመጣል ብለህ የምትሰጋው ነገር አይኑር። የሚገድሉንን ያህል እየሞትን እንጠብቅህሃለን። እመነኝ ስለ ሀገር ሲባል ጥቂት የማይባሉ ንጹሐን በኦሮሚያ ይታረዳሉ። አንተ ሕግ ለማስከበር ከተነሳህ ከዚህ የከፋ የሚመጣ ምንም ነገር አይኖርም። ዐማራ፣ ኦሮሞው፣ ትግሬው ሁሉ ከአንተ ጋር ነው። ሶማሌ አፋር፣ ደቡቡ ከአንተ ጋር ነው። ውር ውር የሚሉትን አትይ። አቋምህ ልምጭ ሆኖ እየተልመጠመጥክ ሰዉ ዝም አለ እንጂ እንደ ምላስህ ብትሠራ፣ ሕግም ይከበር ዘንድ ብትለፋ የሚጠላህ የለም። ችግር ቢመጣም እንኳ መጀመሪያ ሚልዮኖች ከተሰዉ በኋላ ነው አንተ የምትሰዋው። የሃገሪቱ ህዝብ መጀመሪያ ካለቀ በኋላ ነው መሪዋ የሚሰዋው። ደግሞስ ወታደር አይደለህ እንዴ የምን መልመጥመጥ ነው። እናም አቢቹ ሆይ ወጥር። ይሄን የወያኔ የዘር ሰበካ፣ የኤርትራዊው የተስፋዬ ገብረአብ የቡርቃ ዝምታ መርዝ ንፍፊቱን የነፋውን የግብጽ ቅጥረኛና ተላላኪ አሸባሪ አልሸባብ ወፈፌ አትፍራው። የኦሮሚያ ፖሊስ ባይደረብለት እኮ ቄሮ ተብዬውን የአንድ መንደር ወጣት ይበቃው ነበር። ወታደርም፣ ፖሊስም አያስፈልገውም ነበር። ከምር እውነቴ እኮ ነው። ፀረ ኢትዮጵያ ኃይል በኢትዮጵያ ምድር ጉልበት ያለው እንዲመስል ያደረገው እኮ የኦሮሚያ ፖሊስ ነው። ብቻውን የማይንቀሳቀስ፣ ሽንታም ፈሪ። ያለመንጋ አደባባይ የማይወጣ። ቄሮ ከኢ፣ በኢ። ዝረፍ ግደል የሚል ፈሪ ቡድን መድኃኒቱ ከህዝብ ዘንድ ነበር። ግን ምን ያደርጋልነታዲያ ቄሮ ብቻውን አይወጣ። እንደወንድ እጅ ለእጅ አይገጥም። የወሀቢይ እስላም ወጣት ያለ መንጋ አይንቀሳቀስ። ከጀርባው ፖሊስ አዝሎ እኮ ነው እንዲህ የሚፏልለው። ልትመክት፣ ልታስታግሰው ስትነሣ ቄሮ በገጀራ፣ ፖሊስ በጥይት ይነጭሃል። ወይ ነዶ።
•••
እርግጥ ነው ዐማራው አኩርፎብሃል። በብዙ ነገር ከልቡ አዝኖብሃል። የአዲስ አበባ ህዝብም እንዲሁ አኩርፎብሃል። ሲያምኑህ እንደከዳሃቸው ይታወቃል። በጭፍን የሚደግፉህን ጥቂት የአክራሪ ፕሮቴስታንት አማኞችንና በዘር ከረጢት ውስጥ ያሉ ጥቂት ሰዎችን ድጋፍ አይተህ እንዳትሸወድ። ዐማራ የተገፋ ቢሆንም፣ የተበደለ ቢሆንም፣ የተጨቆነ ቢሆንም፣ አሁንም እየታረደ፣ እየተሰቀለ፣ ቢሆንም። ንብረቱን በጠራራ ፀሐይ እያጣ፣ እየወደመበት፣ እየተዘረፈ ቢሆንም ስለ ሃገር ሲል ሁሉን የሚችል አቻዮ ህዝብ ነው። ስለ ሀገር ሲል በምጣዱ ላይ አይጧ እንድታልፍ የሚፈቅድ ህዝብ ነው። እናም ይሄን ህዝብ ያዘው፣ ጠብቀው። አስጠብቀው።
•••
ይሄ አሁን አደባባይ በመንጋ ወጥቶ ሲቀውጥ የነበረውን የተራበና አእምሮውን በወያኔ ትረካ  የተሰለበውን ወጣት ብዙም ኃይልህን አታድክምበት። ቦንብ ሲወረውር፣ ንብረት ሲያወድም፣ ሰው ሲያርድ ዝም ብለህም አትየው። እርምጃ ውሰድበት። ወይም ህዝቡ ራሱን ይከላከል ዘንድ ፍቀድለት። ጠብሶ፣ ጠብሶ፣ አንድዶ ያሳይህ ነበር። ቄሮን ወታደር ፖሊስ ቢተወው፣ ቢለቀው እውነት ኮሮና የተባለው ካለ ሰሞኑን አልጋ ላይ ያውለዋል። በፈጸመው ግፍም እንደቅጠል ያረግፈዋል። ጠብቅ። እንደተባለው ኮሮና የምር ካለ ውጤቱን አብረን ነው የምናየው። እንዲህም ሆኖ ኮሮና በኦሮሚያ ከሌለ ኮሮና ፌክ ነው ማለት ነው። ይኸው ነው።
•••
ቀጣዩ ረሃብ ነው። አንበጣ በሃገሪቱ ዳግም ተከስቷል። አምራች ኃይሉ ሽባ ሆኗል። ምርት ቀንሷል። ብአዴን የህወሓት ተላላኪ ስለሆነ ለአምራች ገበሬው፣ ለሀገር ቀላቢ ገበሬ በወቅቱ ማዳበሪያ አላቀረበም። እናም መጪው ጊዜ አስፈሪ ነው። በኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን በመላው ዓለም አስፈሪ ነው። ከዚያ በፊት ግን የነውጠኞችን ጉረሮ ዝጋ።
•••
ይሄ ኮረና ተብዬ ራሱ ሰሞኑን መልስ ይሰጠናል። እንዲህ ተዛዝሎ ሲሳሳም፣ ሲተሻሽ የነበረ መንጋ በኮሮና ምንም ካልሆነ ኮሬ ቁጩ ናት ማለት ነው። ኮሬ ግን ሰሞኑን ከሌለሽና ካልተገለጥሽ ድሮውንም የለሽም ነበር ማለት ነው። በአሜሪካም፣ በእንግሊዝ በፈረንሳይም ከሰልፉ በኋላ ታማሚም ሟችም አልተነገረም። ቤቱ ተቀምጦ የሞት ዜና ሲዥጎደጎድበ
ት የነበረው ህዝብ አደባባይ ውሎ አድሮ ሲመለስ ዳነ ማለት ነው? በኢትዮጵያም ዶ/ር ሊያ ታደሰ። ቆንጅዬዋ የሞት አብሳሪዋ መልአከ ሞት። ከትናንት ጀምሮ መጥፋትዋ ነው የሚነገረው። እናም ሲነጋ እናየዋለን።
•••
ሌላውን የቀረውን በደህና ጊዜ፣ በሰላሙ ወራት እንነጋገራለን። ካነሰም እያየሁ እጨምራለሁ። መላውን የምታውቁ ይሄን መልእክቴን በፋክስም ቢሆን በፖስታ ከአቢቹ አድርሱልኝ። እንደ ዜጋ የኢትዮጵያ ሀገሬ ጉዳይ ከሚያስጨንቀኝ፣ እንደ አማኝ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከሚያንገበግበኝ ከእኔ ከታላቅ ወንድሙ የተጻፈ ቅን መንፈሳዊ ምክር እንደሆነም ንገሩልኝ። ብሔር የሌለው ንፁሕ የምሥራቅ ሰው የሐረርጌ ቆቱ ነው በሉልኝ። ስትፈልጉ መራታም፣ መቻያም ነው በሉልኝ። ስልጣን፣ ገንዘብ ዝና የማይፈልግ ወንድምህ ነው በሉልኝ። አደራ መልእክቴን አድርሱልኝ። ለኢትዮጵያ ሲባል በጭፍንም ባይሆን ዐብይ አሕመድን ከመደገፍ ውጪ ሌላ አማራጭ የለኝም ብሏል ብላችሁም ንገሩልኝ። አዳራ !   አደራ !  አደራ !
•••
ሻሎም !   ሰላም !  
ሰኔ 24/2012 ዓም
ከራየን ወንዝ ማዶ
Filed in: Amharic