ኢትዮጵያና ከ1966ቱ ‘አብዮት‘ በዃላ የተፈራረቁ መንግሥታት ጠባይ
ናኾም ውብሸት
የቀዳማዊ ኃይለሥላሴን መንግሥት ጨምሮ፣ ከዚያም በፊት የነበሩ የኢትዮጵያ መንግሥታት ኹሉ፣ መንግሥታዊ አስተዳደራቸውን ማዕከል ያደረጉባቸው፣ ሦስት መሠረታዊ የኾኑ፣ ሳይነጣጠሉ ይሠሩባቸው የነበሩ ሕዝባዊ እሴቶች ነበሩዋቸው።እነሱም ሃይማኖት፣ ኢትዮጵያዊ ብሔረተኝነት(Nationalism) እና ባሕል (በውስጡ ቋንቋን፣ ታሪክን እንዲኹም ሀገራዊ ልማዶችን ጨምሮ የተጠቀለሉበት) ናቸው።
ደርግ
የደርግ መንግሥት፣ እራሱን ከሶቭየት ሶሽያሊስት ጎራ ከመደበበት ጊዜ ጀምሮ የተዋሰውን የሶሻሊስት አይዲዎሎጂ፣ የአገዛዙ ዋና መርሑ አድርጐ በመነሳት፣ በባሕልና ቋንቋ በኩል ዐዳዲስ ሶሻሊስታዊ ባሕሎችን ለማስተዋወቅ ቢጥርም፣ ነባርናቀደምት ባሕልን እምብዛም የሚቃረኑ ድርጊቶችን አልፈጸመም። ቋንቋን በተመለከተ፣ ጥሩ ሊባል የሚችል፣ ጉልህ አስተዋጽኦ አድርጓል። የመሠረተ ትምህርት ዘመቻ፣ ለዚኽ ጥሩ ምሳሌ ሊኾን ይችላል። የኢትዮጵያን ብሔራዊ ሉዓላዊነትንበተመለከተም፣ የኢትዮጵያን ብሔረተኝነት(Ethiopian Nationalism)ን ከሶሻሊስት መርሖዎች ጋር አጣጥሞ ለማጐልበትና ለማሳደግ፣ ብዙ ጥሯል፣ የኢትዮጵያ ብሔረተኝነት በኹሉም የኢትዮጵያ ዜጎች ልብ ውስጥ እንዲነሳሳ ሠርቷል። ይኽ ጥረቱለ17ት ዓመታት የፈጸማቸውን ይቅር የማይባል ግፍና በደል ባያስረሳም የሀገር ሉዓላዊነት እና ኢትዮጵያዊ ብሔረተኝነት ላይ ያራምደው የነበረው አቋም እስካሁን ድረስ በሕዝብ ዘንድ እውቅና ያሠጠው ነው። በአንጻሩ የደርግ መንግሥት፣ የኢትዮጵያሕዝብ መልክ የኾነውን ሃይማኖት በመካድና በማዳከም፣ ብሎም ለማጥፋት የሚቻለውን ኹሉ በማድረጉ፣ ከሕዝብ ጋር ልብ ለልብ ሳይገናኝ፣ የሶቭየት ኅብረት ውድቀትን ተከትሎ፣ አየር ላይ ከተንሳፈፈበት የሶሻሊስት አስተሳሰብ ማማ ላይ የሀገሩንአንድነትና ዳርድንበር እንኳን ማስጠበቅ ሳይችል ለውድቀት ተዳርጓል።
ወያኔ-ኢህአዴግ
የወያኔ ኢህአዴግ መንግሥት በተራው ከሦስቱ ጥንታዊት ኢትዮጵያ መንግሥታትና ሕዝብ መገለጫዎች ከኾኑት ኹለቱን ሃይማኖትና ኢትዮጵያዊ ብሔረተኝነትን፣ ክፉኛ ሲዋጋ የኖረና የኢትዮጵያ ሕዝብን ተቀባይነት እስከ መጨረሻው እድሜውሳያገኝ፣ ሕዝብ ዓይንኽን ላፈር ያለው መንግሥት ነበር። የወያኔ መንግሥት፣ በተለይ ኢትዮጵያዊ ብሔረተኝነትን ሲያንቋሽሽና ሲያዳክም፣ የእርስ በእርስ ጎሳን ከጎሳ የሚያጋጩ ሴራዎችን ሲጎነጉንና በዋነኛነት የጎሳ ፖለቲካን ሲያራምድ የነበረ ነው። ለዚኽም ዋነኛ ማስረጃ የሚኾነው፣ ሀገሪቷን በጎሳ በመከፋፈልና ድንበር በማከፋፈል፣ ለእያንዳንዱ ብሔረሰብ፣ የብሔር ፖለቲካን የሚያራምዱ፣ ታማኝ ድርጅቶችን በመፈልፈል፣ ጎሳና ቋንቋን መሠረት ያደረገ፣ ፌደራላዊ የመንግሥት ሥርዓትን መመሥረቱ ነው።
ወያኔ ኢህአዴግ ከጥንስሱ፣ ልክ እንደ ደርግ የሶሻሊዝም አይዲዎሎጂ ፅንሰሐሳብ አቀንቃኝ ስለነበረ፣ ለሃይማኖት ቦታ የለውም ነበር። ሃይማኖትን ለፖለቲካ ዓላማ ለመጠቀም ካልኾነ በስተቀር፣ እንዲዳከምና ብሎም ከኢትዮጵያ ምድር እንዲጠፋ፣በረቀቀ መንገድና በትጋት ሲሠራ ኖሯል። ለዚኽም ጥሩ ምሳሌ የሚኾነው፣ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ የቤተክርስቲያን አስተዳደር መሪነቱን፣ ለፖለቲካው ታማኝ በሆኑ
የወያኔ ኢህአዴግ መንግሥት፣ በእስልምና ሃይማኖትም ላይ፣ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ላይ የተከተለውን የጥፋት መንገድ፣ በተመሳሳይ አራምዷል።
በባሕል ረገድ፣ አንዳንድ ጎጂ ባሕሎችን፣ በተለይ በገጠር ሴቶች ላይ ይደርሱባቸው የነበሩት ጎጂ ባሕላዊ ግዴታዎችን፣ ሕግን በማወጅና በማስከበር፣ ብዙዎቹን ለመቀነስ ብሎም ለማስቀረት ችሏል። ከነዚኽ ውጤታማ ሥራዎቹ፣ እንደ ምሳሌሊወሰድ የሚችለው፣ ልጃገረዶችን ወደትምህርት ቤት እንዲመጡና እንዲማሩ የተደረገው ጥረት፣ በብዛት ያሳየው ስኬታማነት ነው።
በሌላ በኩል፣ በወያኔ ኢህአዴግ መንግሥት፣ ከፍተኛ የባሕል ውድመት የደረሰባቸው ኢትዮጵያዊ የኾኑ ባሕላዊ እሴቶች፣ ብዙ ናቸው ከነዚኽም ውስጥ፣ በጥቂቱ ለምሳሌ ብንወስድ፣ ከፍተኛ የሞራል መላሸቅ፣ ጎሰኝነት፣ ልክ ያጣ ስግብግብነት፣ እራስወዳድነት፣ ዐይን ያወጣ ጉቦኝነት፣ ከዳተኛነት፣ አድርባይነት፣ ይሉኝታ ቢስነት፣ ፍርሃትና ወኔ ቢስነት፣ ልመና፣ ነውረኝነት፣ ሴተኛ አዳሪነት መስፋፋት ይጠቀሳሉ። እነዚኽ ለኢትዮጵያውያን እጅግ አስጻያፊ የነበሩ ምግባሮች፣ በወያኔ ኢህአዴግ ዘመን ክፉኛየተስፋፉበትና የተንሰራፉበት ጊዜ ነበር።
ኦዴፓ-ኢሕአዴግ(ብልጽግና)
ባሕልና ቋንቋን በተመለከተ፣ የኢትዮጵያን ሕዝብ ከኖረበትና በቋንቋ ከሚያስተሳስረው አማርኛ ቋንቋ ለማለያየት፣ አደገኛ የቋንቋ አጠቃቀምና የቋንቋ ትምህርት አሰጣጥ በሀገር ደረጃ ለመዘርጋት ዝግጅት እያደረገ ነው። መጪው ትውልድ በአንድሀገር እየኖረ፣ በቋንቋ የማይግባባበትን ኹኔታን በመፍጠር፣ የጎሳና ቋንቋ ልዩነት የኢትዮጵያን ሕዝብ ወደመለያየት የሚያደርሰውን የኢትዮጵያን የሥራ ቋንቋ ወደ ስድስት ለማሳደግ ድንጋጌዎችንም እያዘጋጀ ነው።
ሃይማኖትን በተመለከተ እንዲኹ ላይ ላዩን ሃይማኖትን አቻችሎ ለማቀፍ የተዘጋጀ ቢመስልም፣ በተቃራኒው የሃይማኖት ግጭቶችን ለሚያባብሱ ለጎሰኞች እና ከውጪ ድጋፍ ለሚያገኙ አክራሪ ሃይማኖተኞች አሉታዊ ነፃነትን(Negative-freedom)በመስጠት፣ በአብዛኛው የሀገሪቱ ክፍል፣ የሃይማኖት ቀውስ እንዲፈጠር ምክንያት ኾኗል። ለዚኽ ማስረጃ የሚኾነው በጅጅጋ፣ በአርሲ፣ በባሌ፣ በሐረር ላለፉት ሁለት ዓመታት በተከታታይ ሲደርስ የነበረው የቤተክርስቲያን መቃጠልና የቀሳውስት ግድያነው። እዚኽ ላይ፣ መንግሥት ይኽን ኹሉ ግፍና ወንጀል አይቶ እንዳለየ ያሳለፈበት ምክንያት፣ መንግሥት እግሩ ሥልጣን ላይ በወጣ ማግስት ጀምሮ የጎበኙትና የጎበኛቸው የዐረብ ሀገራት ካበረከቱት የቢሊዮን ዶላር ሽልማትና ብድር ከሚያስከትለው ድብቅ ተጽእኖ ጋር ሊያያዝ እንደሚችል ይገመታል።
ይኽን የመሰለ የዓለም ሀገራትን ኹሉ ኢኮኖሚ ያናጋ ዓለም አቀፍ ይዘት ያለው የግሎባሊስቶች ማጭበርበር እና የታላላቅ መንግሥታትን መጭበርበር ኹኔታን ስንመለከት፣ በአፍሪካ መንግሥታት አቅም እነዚኽን ግሎባሊስት ዲፕ ስቴት የሚሏቸውን ኃይሎች፣ መጋፈጥ እንዴት ከባድ እንደሚኾን መገመት አያስቸግርም። የኢትዮጵያ መንግሥት፣ አቅምንም ስንፈትሽ ኢትዮጵያ ላይ እነዚኽ ግሎባሊስት ኃይሎች ሊያደርሱ የሚችሉትን ጥፋት ለመከላከል የሚያስችል የደረጀ የቢሮክራሲ አቅምም ዝግጅትም እንደሌለው እንረዳለን። ስለኾነም ያዘዙትን ሳያቅማማ ከመፈጸም ይልቅ በሀገር ውስጥም ኾነ በውጪ የሚገኙ በኽክምናና በሌላ የሞያ ዘርፎች ብዙ ልምድና እውቀት ያላቸውን ባለሞያዎች አሰባስቦ የመጠቀም እንቅስቃሴ ሲያደርግ ተገቢ ይኾናል። ባለፈው ሳምንት በጤና ሚኒስትር መሥሪያ ቤት ትብብር ጭምር የተዘጋጀ ጥናታዊ ጽሐፍ ተብሎ፣ በየዜና አውታሮቹ የተለቀቀው፣ እስከ ሰኔ መጨረሻ ከ28 እስከ 38 ሚሊዮን ሊደርስ የሚችል የኢትዮጵያ ሕዝብ በኮረና ቫይረስ ሊጠቃ ይችላል ብሎ ያስቀመጠው ዳታ ማንኛውም ሪፖርቱን ያነበበና ያዳመጠ ኢትዮጵያዊን የሚያስደነግጥ ነው። በተለይ የቁጥሩ ስሌት መሬት ላይ ካለው ነባራዊ የሀገር ውስጥም ኸኖ የዓለም ኹኔታ ጋር የማይጣጣም መስሎ ስለሚታይ ችላ ሊባል ይችላል፣ ነገር ግን በቢል ጌትስ መሌንዳ BMGF ፋውንዴሽንና ሚካኤል ብሉምበር ጆንኾብኪን ዩኒቨርሲቲ ስኩል ኦፍ ፐብሊክ ሄልዝ አማካኝነት ባለፈው ኦክቶበር 2019 ባልቲሞር ላይ ከተደረገው የ”2019 nCoV” ቫይረስ ሲሙሌሸን፣ ወደ 60 ሚሊዮን የሚጠጋ፣ የዓለም ሕዝብ በቫይረሱ ተጠቅቶ እንደሚሞት ትንበያ ውጤት ጋር አንዲኹም፣ የለንደን ሮያል ኮሌጅ የኮቪድ 19 ሪስፖንስ ቲም በበኩሉ፣ ማርች 17, 2020 ፕሪዲክቲቭ ማቲማቲካል ሞዴልን ተጠቅሞ ባወጣው ግምት መሠረት ግማሽ ሚሊዮን እንግሊዛውያን፣ ሁለት ሚሊዮን አሜሪካውውያን በቀጣዩ ወራት በበሽታው ተጠቅትው ይሞታሉ ከሚሉት ግምቶች ጋር መቀራረቡን ማስተዋል ግን ይቻላል። ይኽን ዘግናኝ ቁጥር በኢትዮጵያ ላይ ሊከሰት ይችላል ተብሎ ተተንብዮ ስናነብ ቫይረሱን ወደ አፍሪካ ሲያመጡት በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ አፍሪካውያንን የመጨረስ አላማ ሊኖራቸው እንደሚችል ያስጠረጥራል። ቢል ጌትስ ፋውንዴሽን፣ አፍሪካ ላይ ትኩረቱን አድርጐ የአፍሪካን ሕዝብ ቁጥር ለመቀነስ እየሠራ ያለ መኾኑን ስናውቅ ደግሞ ስጋታችንን በጣም ከፍ ያደርገዋል። አስር ሚሊዮን የሚቆጠር የአፍሪካ ሕዝብ በቫርይረሱ አፍሪካ ውስጥ ሊሞት እንደሚችልም ገና ከጅምሩ ነበር የገመተልን፣ እ.ኤ.አ 2009 ላይ ደግሞ “የህጻናት ቫክሲኔሽን ላይ ጥሩ ከሰራን የአለምን ሕዝብ ቁጥር ከ10 እስከ 15 ፐርሰንት ልንቀንሰው እንችላለን/If we are doing a real good job vaccinating children, we can reduce the world population by 10% to 15%” (2009 TED talk)። ቢል ጌትስ ፋውንዴሽን በኢትዮጵያ የግብርና ትራንስፎርሜሽን ኤጀንሲ ዋና ስፖንሰር መኾኑን እዚኽ ላይ ማስታወስ ይጠቅማል።
በአጠቃላይ ሲታይ፣ ኦዴፓ ኢህአዴግ መንግሥት፣ የጥንታዊት ኢትዮጵያ መንግሥታት እና ሕዝብ ማንነት የሚያንጸባርቁትን ሦስቱን እሴቶች ያቀፈ የሚመስል፣ ነገር ግን በተቃራኒው እየሠራ ያለ ኾኖ እናገኘዋለን።
እነዚኽ፣ ሦስት፣ ከ1966ቱ ‘አብዮት‘ ወዲኽ የተፈራራቁ መንግሥታት፣ በአንድም ኾነ በሌላ መልኩ ሦስቱን ኢትዮጵያዊ ሕዝባዊ እሴቶችን በአንድ ላይ፣ በአስተዳደራቸው ውስጥ ማስተናገድ ስለተሳናቸው፣ የሕዝብን ልብ ማሸነፍ አልቻሉም። በዚኽም ምክንያት፣ መላውን የኢትዮጵያ ሕዝብ፣ በአንድ ልብ ከጐናቸው ለማሳለፍና ለሀገር ኹለንተናዊ እድገት ሊውል የሚችልን ትልቅ አቅም ለመገንባትና ለመጠቀም ሳይችሉ ቀርተዋል።
ኹሉን የሚያይ ኃያሉ እግዚአብሔር ሀገራችንን ከክፉ መዓት ይጠብቅልን!!!
አሜን!