መ/ታሪኩ አበራ
† ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ከዕንቁ የከበረች ነች።†
† የራሻ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን በከተማና በገጠር በየጎዳናው ጸሎተ ዕጣን በማድረስ አጋንንትን እያስጨነቀች የሕዝቧንም ሥነ ልቡና ከጭንቀትና ከሥጋት እያላቀቀች በኢየሱስ ክርስቶስ ኃይለ መስቀል በእምነት እያበረታች ነው ።†
እምነት ቀልድና ተራ ነገር አይደለም እንደ ወርቅ በእሳት የሚፈተን የክብር ዘውድ ነው። ሌሎች ቤተእምነቶች በሰላሙ ጊዜ ተአምራትና ፈውስ እናደርጋለን እያሉ በየአዳራሹ ጤነኛ ሕዝብ ላይ ሲቀልዱና ሲያጭበረብሩ ውለው ያድራሉ እውነተኛው ደዌና እውነተኛ ሕሙማን ሲመጡ ግን እግሬ አውጭኝ ብለው ፈርጥጠው ይጠፋሉ ምክንያቱ አማኞች ሳይሆኑ አስመሳዮች ናቸው። እምነት በእውነተኛ የመከራ ቀን በችግር ላይ የእምነትን አዋጅ አውጆ በኃይልና በሥልጣን መውጣት ነው። ኃይል የእግዚአብሔር ነው።ድሉም የኦርቶዶክሳውያን ነው።
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያንም በታላቅ እምነት እግዚአብሔርን እየተማጸነች በምህላ፣በጸሎተ ዕጣን የአጋንንትን ውጊያ ድል እያደረገች ነው።ክብር ሁሉ በሰማይና በምድር ለልዑል እግዚአብሔር ይሁን።
15፤ የእምነትም ጸሎት ድውዩን ያድናል ጌታም ያስነሣዋል፤ ኃጢአትንም ሠርቶ እንደ ሆነ ይሰረይለታል።
16፤ እርስ በርሳችሁ በኃጢአታችሁ ተናዘዙ። ትፈወሱም ዘንድ እያንዳንዱ ስለ ሌላው ይጸልይ፤ የጻድቅ ሰው ጸሎት በሥራዋ እጅግ ኃይል ታደርጋለች።
17፤ ኤልያስ እንደ እኛ የሆነ ሰው ነበረ፥ ዝናብም እንዳይዘንብ አጥብቆ ጸለየ፥ በምድርም ላይ ሦስት ዓመት ከስድስት ወር አልዘነበም፤ ሁለተኛም ጸለየ፥
18፤ ሰማዩም ዝናብን ሰጠ ምድሪቱም ፍሬዋን አበቀለች።
እግዚአብሔር ምድራችንን በልጁ ደም ይፈውሳት።