>
5:13 pm - Wednesday April 20, 3340

የገበሬ ላብ ያደለባት እሌኒ ገ/መድህን (ካሳ አንበሳው)

የገበሬ ላብ ያደለባት እሌኒ ገ/መድህን

 

ካሳ አንበሳው
ዜጎችን በማራቆት የህወሓትን የኢኮኖሚ ጡንቻ ካፈረጠሙ ሰዎች መካከል ዘመዴነህ ንጋቱን እና እሌኒ ገ/መድህንን የሚስተካከል አይገኝም፤ የኢትዮጵያን ገጸ-ምድር እና ከርሰ-ምድር ዶላር መክፈል ለሚችል ለውጭ ዜጋ አሻሽጦ ሰለከበረው፣ የወያኔ ባለስልጣናትን የገንዘብ ባህር ውስጥ ስለነከረው፣ ዜጋውን የደም እንባ ስላስለቀሰው ዘመዴነህ ንጋቱ ከዚህ ቀደም የተወሰነ ብያለው፤ ዛሬ የእሌኒ ገ/መድህንን ሸፍጥ በጥቂቱ ልንገራችሁ::
ስሟ በብዛት የሚነሳው የኢትዮጵያን ምርት ገበያ ድርጅት (ECX) ጋር ተያይዞ ነው፤ ሙሉ ስሟ እሌኔ ዘውዱ ገ/መድህን ይባላል፤ የተወለደችው አዲስ አበባ ሲሆን ዜግነት ከሲዊዘርላንድ ወስዳለች፤ በስታንፎርድ፣ በሚችጋን እና በኮርኔል ዩኒሸርስቲዎች ትምህርቷን ተከታትላለች፤ [don’t let her qualifications fool you; keep on reading]፤ ኢትዮጵያ ከመግባቷ በፊት ለአለም ባንክ ሰርታለች፤ ወደ ሀገር ቤት ያመጣትን ጉዳይ ስትገልጽ <<የኢትዮጵያን የንግድ ስርዓት መልክ እንዳሲዝ ከጠ/ሚ መለስ ዜናዊ ጥሪ ደረሰኝ>> ትላለች፤ ጥሪውን ተቀብላ ጨርቄን ማቄን ሳትል ወደ አዲስ አበባ አቀናች፤ ጠቅላይ ሚንስቴሩ ጽ/ቤት አንድ ቢሮ ተሰጥቷት ስራዋን ጀመረች፤ የኢትዮጵያን ምርት ገበያ ድርጅት (ECX) ተብሎ የሚጠራው ድርጅት በዚህ መልክ ተጸነሰ፤ እሌኒ እና መለስ ቢሮ ዘግተው የጸነሱት ይህ ድርጅት የዛሬ 12 ዓመት በአዋጅ ቁጥር 550/2000 ተወለደ፤ ይህ ድርጅት ምንም አይነት ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ (Macro Economic Significance) እንደሌለው በተለያዩ ምሁራን ተነግሯል፤ ጊዜ ያለው ከስር በተራ ቁጥር አንድ ላይ ያለውን ማስፈንጠሪያ ተከትሎ ፕሮፌሰር ሰይድ ሀሰን “The dangerous hype behind Ethiopian Commodity Exchange” በሚል ርዕስ ያተሙትን ጽሑፍ ያንብብ፤ የዚህ ፕሮፌሰርና የሌሎች ምሁራንን ክርክር ወዳጄ Meskerem Abera ከሁለት ቀን በፊት “እሌኒ ገብረ መድህን መጋዘን ከመገንባት ያለፍ ምን ሰርታለች?” ስትል በተጠየቅ ዘግታዋለች፤ እኔ ደግሞ ከመጋዘኑ ስር የዘረፋ መዋቅር ዘርግታለች እላለሁ፤ ይህን ገለጥለጥ አድርገን እንመልከት፤
የECX ዋና ተግባር በመላ ኢትዮጵያ የሚመረቱትን የቡና፣ ጥራጥሬ እና የቅባት እህሎችን ለውጭ ገበያ አቅራቢዎች ማጫረት ነው፤ በመጀመሪያ የቡና፣ ጥራጥሬ እና የቅባት እህሎች ተሰብስበው ECX መጋዘን ይገባሉ፤ በመቀጠልም የጥራት ደራጃ ይወጣላቸዋል፤ በመጨረሻም የመነሻ ዋጋ ይሰጣቸውና የድርጅቱ አባል የሆኑ ላኪዎች እንዲጫረቱ ይደረጋል፤ ከፍተኛ ዋጋ የሚሰጥ ላኪ አሸንፏል ተብሎ ጨረታው ይዘጋል፤ የዚህ ድርጅት አባል እና ተጫራቾች የህወሓት እና የህወሓት አጋፋሪዎች መሆናቸው የአደባባይ ሚስጥር ነው፤ በብሉንበርግ (bloomberg) ዘገባ መሰረት የኢትዮጵያን የብና እና የቅባት እህሎች በዋነኝነት ለውጭ ገበያ እያቀረበ ያለው የኢፈርቱ ጉና ትሬዲንግ ነው፤ በአጭሩ ECX የጉና መጋዘን ነው ብንል ከእውነቱ አንርቅም፤ የሀገሪቱን ጠቅላላ የውጭ ንግድ በዚህ መልኩ በአንድ እዝ አስገብታ ስታበቃ ህወሓትን እነሆ በረከት አለችው፤ ECX ምን ያህል በሙስና የነቀዘ መሆኑን ለመረዳት ከስር በተራ ቁጥር 2 ላይ የተሰጠውን ማስፈንጠሪያ ተከትለው ያንቡ::
ይህ የይስሙላ ጨረታ ሳያያቸው የውሃ ሽታ የሚሆኑ ምርቶች ቁጥር ስፍር የላቸውም፤ የዛሬ 8 ዓመት ገደማ 10 ሺህ ቶን (10 ሚሊየን ኪሎ) ቡና ከECX መጋዘን ጠፋ ተባለ፤ ምጥ ይግባ ስምጥ አልታወቀም፤ ይህ ያበገናቸው ውስጥ አዋቂዎች ጉዳዩን ለግል ጋዜጦች ሹክ አሉ፤ በአለም አቀፍ ደረጃም መነጋገሪያ ሆነ፤ ይህን ጊዜ መለስ ዜናዊ በቴሌቪዥን ብቅ ብሎ <<ያለፈው አልፏል ከንግዲህ መደገም የለበትም>> ብሎ ፋይሉን ዘጋው፤ ከስር በተራ ቁጥር 3 ያለውን ማስፈንጠሪያ ተከትለው የመለስን መልስ ይመልከቱ::
የዛሬ አመት ደግሞ 19 ሺህ ቶን (19 ሚሊየን ኪሎ) ቡና ከእሌኒ መጋዘን እንደጉም ተኖ ጠፋ ተባለ፤ ይህን አስመልክቶ አዲስ ዘመን ጋዜጣ የሰራውን ሪፖርት ከስር በተራ ቁጥር 4 ያለውን ማስፈንጠሪያ ተከትለው ያንቡ፤ ከሁሉ የሚገርመው ለይስሙላ እንኳን ህግ ፊት የቀረበ ሰው አለመኖሩ ነው፤ እንግዲህ እነዚህ ለሚድያ የበቁ ዘረፋዋች ናቸው፤ የወያኔ መንግስት ሲገረሰስ የሚጋለጡ ብዙ ዘረፋዎ እና ምዝበራዎች መኖራቸው አይጠረጠርም::
ለማንኛውም የወያኔ መንግስት ወደ መቃብር ሲወርድ ካቴን ከሚጠልቅላቸው ውስጥ እሌኒ ገ/መድህን ከፊት መስመር ትገኛለች፤ ይህ እንደሚመጣ ስለሚያውቁ እሌኒም ሆነች ዘመዴነህ የውጭ ዜግነታቸውን ሳይመልሱ አድፍጠው እየጠበቁ ነው፤
እሌኒ ዛሬ ምን እየሰራች ነው?
ለዚህ ጥያቄ አጭሩ መልስ “ዛሬም ደም እየመጠጠች ነው” የሚል ነው፤ ዛሬ ደግሞ “BlueMoon” ተብሎ የሚጠራ shady business ከፍታለች፤ ግብረ ሰናይ ድርጅት (civil organization) ይሁን የግል ኩባን የሚታወቅ ነገር የለም፤ የግብርና ንግድ (agribusiness) ላይ ነው የምሰራው ትላለች፤  በዚህ ዘርፍ የሚታይና የሚዳሰስ ነገር ግን አታሳይም፤ የድርጅቱ ድረ ገጽ ላይ የሚታየው የሚከራዩ የስብሰባ አዳራሾች ከነ ዋጋቸው ነው፤
ከስር ፎቶው ላይ እንደሚታየው አጋሮቼ የምትላቸው ግዙፍ የምግባረ ሰናይ ድርጅቶች ናቸው፤ ሌሎቹን እንተዋቸውና Save the Children የግብርና ገበያ ውስጥ ምን ይዶለዋል?? የከፈተችው የምግባረ ሰናይ ድርጅት ነው እንዳንል ህዝቡን ስትረዳ አይቻለው የሚል ተፈልጎ አልተገኝም፤ ቁጥጥር የሚያደርግ የመንግስት አካል የለምና እሌኒ እንዳሻት እየሆነች ነው፤ በዚህ ሁሉ ውስጥ አንድ ነገር በእርግጠኝነት መናገር እችላለሁ፤ ከአለም አቀፍ የእርዳታ ድርጅቶችና ኢንባሲዎች በኢትዮጵያ ህዝብ ስም በሚሊየን የሚቆጠር ዶላር እየሰበሰበች እንደሆነ በልበ ሙሉነት መናገር እችላለሁ፤
በመጨረሻም:-
እሌኒ አብይን ጎሸም ማድረጓ ሊገርመን አይገባም፤ ወደ ፊት በአይጋ ፎረም ወይም በሌላ ሚዲያ ስራዓቱን የሚያጠለሽ ጽሑፍ ማውጣቷ አይቀርም፤ ይህ ደግሞ የአብይ መንግስት ወደ ቅልቡ ተመልሶ የበላሽውን ትፊ፣ በወንጀልሽ ተቀጭበት ያለ ጊዜ የታሰርኩት ሀሳቤን በመግለጼ ነው ለማለት ይጠቅማታል፤ [በነገራችን ላይ በወያኔ ዘመን በተለይ ዲያስፖራውን የሚወቅጥ ጽሑፍ አይጋ ፎረም ላይ ታወጣ ነበር]
2. https://ecadforum.com/…/the-case-of-alleged-fraud-and-corr…/
4. http://www.ethpress.gov.et/…/…/business-market/item/11136-19
Filed in: Amharic