>

የሱማሌ ወራሪ ጦር መቅሰፍት ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ !!! (ዮናስ አበራ)

የሱማሌ ወራሪ ጦር መቅሰፍት ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ !!!

ዮናስ አበራ
ሁለት የሶማሌ የጦር አውሮፕላኖችን መተው የጣሉት የቀድሞ አየር ኃይል ጀግና !!
ኮለኔል ባጫ ሁንዴ 
ኮለኔል ባጫ ሁንዴ በአንቦ አካባቢ በጊንጪ ከተማ ተወለዱ ።በአምቦ ከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን እንዳጠናቀቁ በ1965 እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር በኢትዮጵያ አየር ሃይል በአውሮፕላን ጥገና አገራቸውን ለማገልገል ተቀጥረው ስልጠናቸውን እንደጨረሱ ከክፍላቸው ያመጡት ውጤት የላቀ በመሆኑ እና የተዋጊ አውሮፕላን በራሪ ለመሆን ባሳዩት ከፍተኛ ፍላጎት ሙያው የሚጠይቀውን ማንኛውንም መስፈርት በማሟላት ወደ በረራ ትምህርት ቤት ገቡ።
የሚፈለግባቸውን የበረራ ትምህርት እንደጨረሱ ወደ ተዋጊ ስኳድሮን በመመደብ የኤፍ 86 አውሮፕላን ሲበሩ ቆይተው የኢትዮጵያ አየር ሃይል F-5E የሚባል አዲስ አውሮፕላን ሲገዛ ወደ አሜሪካን አገር ተልከው በዚሁ አውሮፕላን ስልጠና በመውሰድ እና በማጠናቀቅ ወደ አገራቸው ተመልሰው በወቅቱ አገራችንን የወረሩትን የሱማሌ ወራሪዎች ጋር ፍልሚያ ውስጥ በመግባት በአየር ላይ ውጊያ ( Dog fight) ሁለት የሱማሌ ሚግ አውሮፕላኖችን መትተው የጣሉ ሲሆን በዚህም ላሳዩት ከፍተኛ ጀግንነት ከኢትዮጵያ መንግስት የጦር ሜዳ የላቀ ጀግንነት ሜዳይ ተሸላሚ ሆነዋል።
ኮለኔል ባጫ በወቅቱ በነበረው የኢትዮጵያ መንግስት አስተዳደር ባለመደሰት በ1986 ሲሲና የምትባል አውሮፕላን በማብረር ወደ ሱዳን ተሰደው በመጨረሻም ወደ አሜሪካ በመምጣት በሳንፍራንሲስኮ ከተማ ህይወታቸው እስካለፈበት ቀን ድረስ ኖረዋል።
ኮለኔል ባጫ የአንድ ሴት እና የሁለት ወንዶች አባት ሲሆኑ ሶስት የልጅ ልጅ ለማየትም በቅተዋል። ነብስ ይማር ጀግናዬ።
PS:
 የቀደሞዎቹ ስርዓቶች ኦሮሞን ያገለሉ ነበሩ እያልክ ወያኔ ፅፎ የሰጠህን ተረት ተረት ይዘህ መንደር ለመንደር እየዞርክ “ነፍጠኛ ጨቆኖኛል” እያልክ ስትበጠረቅ ትውላለህ !! በጥራቃ !! ገና ብዙ ጉድ እንፈለፍላለን !! በገዛ እጅህ ነካክተኸናል!! አሳ ጎርጓሪ ….
Filed in: Amharic