>

የዘንድሮ የህወሓት(ሂዊ) አስደንጋጭ፣ አሳፋሪና አስደማሚ ሁነቶች!!! (ሉቃስ አንደርሰን)

የዘንድሮ የህወሓት(ሂዊ) አስደንጋጭ፣ አሳፋሪና አስደማሚ ሁነቶች!!!

ሉቃስ አንደርሰን

1ኛ) ስብሰባ ረግጦ መውጣት!
2ኛ) ከስብሰባ በአድማ መቅረት!
3ኛ) ፈርታ መቀሌ መሰግሰግ!
4ኛ) አጫፋሪዎች ከጎኗ ማጣት!
5ኛ) በታሪኳለ45 አመታት አድርጋው የማታውቀውን አስቸኳይ ጉባኤ መጥራት!
6ኛ) የምትኮራበት ስንቱን የሾመችበት የሸለመችበት የገደለችበት ያስገደለችበት የሰረቀችበት ያሰረቀችበት ኢህአዴግን ከአይኗ ስር ሲተን እያየች ማልቀስ የጀመረችበት!
7ኛ)ትናንት ተቃዋሚ አሸባሪ እያለች ስታስር ስታሳድዳቸው ለነበሩ ፓርቲዎችና ግለሰቦች አፋሽ አጎንባሽ መሆኗ
8ኛ) መደመሩም እዳ መቀነሱም ጣጣ ሆኖባት መቸገሯ
9ኛ) ዙሪያውን በራስ ሰውና በገዳይ ስኳድ ያጠረችውን ስልጣን “ተቀበሉኝ እንጂ አትንጠቁኝ፤ ቀይዋን መስመር እንዳታልፉ…”  ዛቻና ማስፈራሪያዋ ሰሚ ማጣቱ
10ኛ) በደም አመጣሁት ያለ ደም አልልቀውም ያለችውን ስልጣን ከሰመመን እንቅልፏ ስትነቃ በተረኞች መዳፍ ላይ ማየቷ
12ኛ) “የደፈሩትን እደፍራለሁ አልደራደርበትም” ያለችው ህገ መንግስት በተረኞች ሲደፈር ማየቷ
13) ትናንት በቀጭ ትእዛዝ ከመቀሌ ወደ ቃሊቲ ዘብጥያ የወረወረቻቸው የቤተ መግስቱ ቤተኛ ሆነው ጫማ እንለካካ ሲሏት ማየቷ።
14ኛ) በጀቷን በመጀመሪያ ሩብ አመት የጨረሰችበት (ይሄ እንኳን ድሮ የቺክ እና ውስኪ ወጪ ከፌደራሉ ነበር አሁን ከክልል ሆነ ውይይይይ!
15ኛ) ለምርጫ ቅስቀሳ በፌደራሉ በጀትና መኪና ማድረግ አለመቻሏን ማየቷ!
16ኛ) ውሽሞቿ ኢቢሲ ፋና እና ዋልታን የተነጠቀችበት በነገራችን ላይ የውሽማ ነገር ሲነሳ ብዙ ውሽሞቿ ያኮርፋሉ እኔ ልደቱ እና በቀለ ጀዋር ምናምን አላልኩም።ይሄ ደሞ ማን ነው ድንግል ውሽማዋ አዎ አሰፋ ወዳጆን ያገኘችበት
17ኛ) አቦይ ስባሃት የኤፈርትን ብር አልሰጥም ያሉበት ¨እወይ ተቃጢልና! ¨ አለች ህወሓት ችግሩ ሲበረታባት ድህነት  ሲልጣት
Filed in: Amharic