እንኳን ደስ ያለህ!
ጌታቸው አበራ
(ለመቶኛው የኖቤል የሰላም ሎሬት ለ ዶ/ር ዐብይ አህመድ)
የሰው ዘር የምንጭ ህይወት – የዘመናት ታሪክ እናት፣
የነጻነት ቀንዲል ብርሃን – ያለም ማማ የእግዚአብሔር ቤት፤
የመለኮት ምስጢራቱ – ቅድስት አገር ኢትዮጵያ፣
መከራዋን አሸንፋ – ባለም ታየች ሃሌሉያ!
…ከበሻሻ መደብ–አልጋ – የተነሳው ብላቴና፣
ቀጭን መንገድ በድክ ድክ – ውጣ–ውረድ.. አለፈና፣
በሰንበሌጥ ተመስሎ – ጎርፉን አልፎ ለጥ ብሎ፣
አሳር፣ ችግር፣ ሞትን ከድቶ – በተዐምር ህይወት ዘርቶ፣
ካለም ጫፍ ላይ በድል ታየ – የክብር አክሊል ወርቁን ደፍቶ።
ያገር አድባር ግዙፍ ዋርካ፣
ስኬት ተስፋው እሚለካ፣
የይቻላል ትምህርት ቤት – ለትውልዱ አርአያ፣
ክብር ኩራት ለናት አገር ለእምዬ ለኢትዮጵያ!
ጌታቸው አበራ
ህዳር 2012 ዓ/ም
(ዲሴምበር 2019)