>
5:13 pm - Monday April 19, 6579

 ስለ አቦይ ሥብሃትን ማንነት ልንገራችሁ ( ዮሀንስ አያሌው)

ስለ አቦይ ሥብሃትን ማንነት ልንገራችሁ
ዮሀንስ አያሌው
” ደመቀ የሸወደንን ያክል መሰሪው ጀበሃ (ሻእቢያ) እንኳን አልሸወደንም!” 
አቦይ ስብሀት ነጋ
 
ደመቀ ለትህነግ ታማኝና ታዛዥ ነበር። ፈፅም! የተባለውን ነገር ለመፈፀም ‘ ለምን? ‘ ብሎ እንኳን አያውቅም። አንድ ቀን ግን የሱዳን ግዛት የሆነውን አዋሳኝ መሬት ለመስጠት ፈርም ሲባል ና “አይሆንም አልፈርምም!” ብሎ አሻፈረኝ ሲል ያኔ ይህ ሰው አንድ ቀን እንደሚሸውደን እርግጠኛ ሁኜ ለጓዶቼ ነግሬያቸው ነበር። ሁሉም የእኔን እይታ ሳያቅማሙ ሲቀበሉኝ  #ጌታቸው ግን አታስብ እሱ መዳፋችን ውስጥ ነው። የትም አይደርስም!” ብሎ በንቀት ሲመልስልኝ ሲሰሙ ጓዶች በጌታቸው ላይ ከፍተኛ እምነት ስለነበራቸው እነሱም ወደጎን ተውት።
     እኔ ግን “ጀግናን የሚገድለው ተራ ወይም የተናቀ ሰው ነው።” ብየ ጌታቸውን አስጠንቅቄው ነበር። የመጨረሻው የጠ/ሚ የውድድር እለት ዋዜማ ማታ ላይ በነበረን ስብሰባም ይህ ሰው አንድ ነገር እንዳያደርግ በሚል ጥሩ ስሜት እንደማይሰማኝ ስናገር በተለይ ጌታቸው አሰፋ፣ ጌታቸው ረዳ ና አቦይ ፀሀየ “አትጨነቅ ደመቀ በሚገባ አምኖበታል። የተባለውን ባያደርግ የሚደርስበትንም
ያውቃል ። በተጨማሪ ደግሞ ሁሉንም የብአዴን፣ የኦህዴድ ና የደህዴን አባላት ቀጣይ የከፍተኛ ሚኒስትርነት ስልጣን ና ዳጉስ ያለ ገንዘብ እንደሚሰጣቸው በራሳቸው ሰዎች ስለተነገራቸው በደስታ ተቀብለውታል። ” ብለው ሊያሳምኑኝ ሞከሩ። በእርግጥም በተለይ የደህዴንና የብአዴን አመራሮች ለስልጣንና ለጥቅም የማይከፍሉት ዋጋ እንደሌለ በማስረጃ ሲያስቀምጡልኝ ባላምንበትም ይሁን ብየ ተውኩት።
     በትጥቅ ትግል ወቅትም ሆነ በስልጣን ላይ ከሆንን በኋላ ድርጅቴ ሊደርስበት ከተጋረጠ እስከ መፍረስ የሚያደርስ ከፍተኛ አደጋዎች በአለቀ ሰአት እንኳን እንደታደግሁ ስለሚያውቁኝ ይቀበሉኛል ብየ ተስፋ አድርጌ ነበር። አሁን ግን ከእኔ ውጪ የእኔን ሀሳብ የሚያስብ ና የሚደግፈኝ  ሰው ሳጣ ዝም ብየ ቁጭ አልኩና የሚሆነውን ለማየት ወሰንኩ። በመጨረሻ ግን ለረጅም አመታት በነበረን የትጥቅ ትግል መሰሪው ጀበሃ(ሻእቢያ) እንኳን ሸውዶን የማያውቀውን ሽወዳ #ደመቀ #ሸወደን! አዋረደን! ለዚህ ውድቀታችን ተጠያቂዎች ሁለቱ ጌታቸው የተባሉትና ፀሀየ ናቸው።  “
    አቦይ ስብሀት ዶ/ር አብይ በተመረጡ ማግስት ለትህነግ አመራሮች በመቀሌ ከሰጡት አስተያየት ከትግረኛ ወደ አማርኛ የተቀየረ።
ስለ አቦይ ሥብሃትን ማንነት ልንገራችሁ
     እኚህ የ84 አንጋፋ ሽማግሌ ለ40 ዓመት ወያኔን እና ሻቢያን እያስተዳደሩ ኖረዋል .. አሁን መሞቻቸው እየደረሰ ስለሆነ ቀጣይ የሁለቱ ድርጅቶች እጣፈንታ ምን እንደሆነ መገመት አያቅትም…..
       የስብሃት አባት ፊታውራሪ ነጋ ከተለያዩ ሚስቶች የሚወለዱ 18 ልጆች ወልደዋል..
እኚህ ሰው በትግራይ አድዋ አውራጃ አዲያቡ ገዢ ነበሩ፡፡በድሮው ጊዜ በትግራይ አካባቢ ባንዳነት ትልቅ ስራ ነበር እና እሳቸውም ትልቅ ባንዳ ነበሩ፡፡የአቶ ስብሃት የእናት ወንድም በኢጥዮጵያ ውስጥ ታዋቂ ባንዳ ተክሉ መሸሻ ይባላሉ.. የፊታውራሪ ነጋ ልጆች በከፊል.. በላይ ነጋ ፣ስብሃት ነጋ፣ ገ/እግዛቤር ነጋ፣ዮሴፍ ነጋ፣ወልደሩፋኤል ነጋ፣አቤሴሎም ነጋ፣እስጢፋኖስ ነጋ፣ቅዱሳን ነጋ፣እቴነሽ ነጋ፣አበራሽ ነጋ፣ሃይሌአባይ ነጋ፣…..ይቀጥላል ሁለቱ ሞተዋል 16ቱ 32 ሆነው ሁለቱን ሃገሮች ፐሮፋይላቸውን ደብቀው እየጨፈጨፉ እየኖሩ ነው፡፡ ሁሉም ባለስልጣን እና ሃብታሞች ናቸው..
     ህውሃትን መጀመሪያ ከስብሃት በፊት የመሰረተው ገሰሰ አየሎም ነበር.. ስብሃት ነው የገደለው.. ቀጥሎ አረጋዊ በርሄን ሊገለው ሲል አምልጦ አሜሪካ ገባ..
የዚህ ሰው ታናሽ እህት ቅዱሳን ነጋ የፀጋየ በርሄ ባለቤት ናት.. ፀጋየ በርሄ ቀድሞ የትግራይ ገዢ ነበር. ትግራይን በሚፈልጉበት መንገድ አዋቅረው ነው የመጡት..ፀጋየ በርሄ አሁን የመከላከያ እና ደህንነት ጉዳይ አላፊ ነው..ሳሞራም ሆነ ጌታቸው ሪፖርት የሚያደርጉት ለሱ ነው.. ቅዱሳንም ነጋም በህውሃት የሴቶች ተጠሪ ናት.. አዜብ መስፍንን ጨምሮ ሁሉን ነገር ሪፖርት የሚያደርጉት ለአዜብ ነው..
የገ/እግዛቤር ነጋ ልጅ ፈትለወርቅ ገ/እግዛቤር የአባይ ፀሃዬ ባለቤት ነች.. አቤሴሎም ነጋ እዚህ ዘርፎ በአውስትራልያ ቢሌነር ነው .. ሌሎቹም እንዲሁ ገና ሃገራችን ኢትዮጵያ ባጥንትዋ እስክትሄድ ድረስ እየዘረፉ ናቸው፤፤
     የስብሃት ነጋ ቤተሰብ ኤርትራም ይዘልቃል.. የኢሳያስ አፈወርቅ ፀሃፊ አበራሽ ነጋ ትባላለች .. ያለ እሱዋ ፈቃድ ኢሳያስን ማግኘትም ማነጋገርም ኤቻልም. ሻቢያ ምን እንደሚሰራ የምታው ቅ ፈላጭ ቆራጭ እሱዋ ናት.. ይችሰው የኢሳያስ ሁለተኛው ሰው ጀነራል ስብሃት ኤፍሬም ባለቤት ነች..4ልጆችን ወልዳለታለች…
    ሌላው በኤርትራ የኢትዮጵያ ተቃዋሚ የተባሉትን የድራማው አሻንጉሊቶች የሚቆጣጠር፣ የሚያሰለጥን፣ መሳሪያ የሚያቀርበው ሰው ጀነራል ፍፁም ( በቅጥል ስሙ ወዲ መቐለ)ይባላል.. የአቦይ ስብሃት የሚስቱ ወንድም ነው፡፡
Filed in: Amharic