>
5:13 pm - Tuesday April 19, 6991

በአዲስ አበባ ባንዲራ ይዞ መታየት ለፖሊስ ዱላና እስር እየዳረገ ነው!!! (የአሃዱ ሬዲዮ ጋዜጠኛ ትእግስት ታንቱ)

በአዲስ አበባ ባንዲራ ይዞ መታየት ለፖሊስ ዱላና እስር እየዳረገ ነው!!!
የአሃዱ ሬዲዮ ጋዜጠኛ ትእግስት ታንቱ
” ባልደራስ ነው የላከሽ! ” 
መርማሪ ፖሊስ
     ጥዋት 3:00 ገደማ ቢሮ ልገባ ታክሲ ይዤ ፒያሳ ደረስኩ ኦይል ሊቢያ አካባቢ ግርግር ተፈጥሮ ብዙ ሰዎች ተሰብስበዋል ። እኔም ሰዎች ወደ ተሰበስቡበት ተጠጋው ከዚያ ማህል ላይ አንድ ወጣት እድሜው በግምት 28 – 30 የሚሆነው ኮከብ የሌለውን ባንዲራ ይዞ ይገኛል ይህን ወጣት “ባንዲራ ለምን ያዝክ?” ከዚያሚሉ ከፖሊሶች ጋር በተፈጠረ አለመግባባት ነው ግርግሩ የተፈጠረው ።
     ፖሊሶቹም ልጁን ” ወደ ፖሊስ ጣቢያ እንሂድና እዛው እናወራለን ” ሲሉት ” አልሄድም ምንም አላደረኩም ” በሚል ነገሩ እየተካረረ መጣና ወጣቱን መደብደብ ጀመሩ ቦታው ላይ የነበሩ ሰዎች “አትመቱትም” በሚል ተከራከሩ ከዛም ከዚህም ፎቶ የሚያነሱ ሰዎች ነበሩ አይናቸው ያረፈው እኔ ላይ ሆነ ሶስት ፖሊሶች መጥተው ” ፎቶ ማንሳት ወንጀል ነው አንቺም ትታሰርያለሽ! ወደ ፖሊስ ጣቢያ ትሄጅያለሽ!” ብለው አዋከቡኝ ። እየገፈተሩና እየጎተቱም ወደ መኪናቸው አስገቡኝ ።
   ባንዲራ የያዘውን ወጣትና  ኔን ይዘው ፒያሳ ጣይቱ ሆቴል አካባቢ ወዳለው ፖሊስ ጣቢያ ወሰዱን ።ከዚያም በቁጥር 6 የሚሆኑ ፖሊሶች እየተቀባበሉ ክፉኛ ደበደቡት! ወደ እኔም ዞረው ሁለቴ በጥፊ ከመቱኝ በኋላ ” ሴት መሆንሽ ነው ያተረፈሽ! ” ብለውኝ ተበታተኑ።
መርማሪ ፖሊስ ወደ ውስጥ እንድገባ አዞኝ ገባሁ፣ አንዱ መጥቶ ” ባልደራስ ነው የላከሽ! ” ሲላት ሌላኛው ደግሞ ” ልታስበጠብጪ ፈልገሽ ነው!” ብለው ያነሳውትን ፎቶ አጠፉ። የማስጠንቀቂያ አይነት ሰተውኝ ተለቀቅኩ። ወጣቱ ላይ የሚደርሰውን መገመት ይቻላል።
Filed in: Amharic