አቻምየለህ ታምሩ
የዐፄ ፋሲል ዘውድ የኢትዮጵያን አሻራዎች ማጥፋትን ለኦሮሞ ተቆርቋሪ መሆኑን እንደማሳያ አድርጎ ለያዘው ኦነጋዊ አገዛዝ ተላልፎ ሊሰጥ አይገባም!
ከዛሬ 353 ዓመታት በፊት በተወለዱ በ78 ዓመታቸው መስከረም 15 ቀን 1659 ዓ.ም ከዚህ ዓለም ያለፉት ታሪካዊቷን ጎንደር ከተማን የቆረቆሯት የዐፄ ዘውድ በሀገረ ሆላንድ ተገኝቷል። ዘውዱ በኢትዮጵያ አቆጣጠር የተሰራበትን ዘመን ፲፮፻፳፮ [1626] ዓመተ ምሕረት በመጥቀስ ዘውዱ የማን እንደሆነ ሲገልጽ «በዐፄ ፋሲል ዘመነ መንግሥት» የሚል በኢትዮጵያ ፊደል ታጽፎበታል።
የዐፄ ፋሲልን ኢትዮጵያ የወሰን ልክ ለማወቅ እንዲህ ተብሎ ከተገጠመላቸው ቅኔ መገንዘብ ይቻላል፤
ጎንደር ቢያጉረመርም ፋሲል ፈረስህ፣
ኑብያና ስናር ወርቁን ጫኑልህ፡፡
ሳሩን ተጠየፈ የፋሲል ፈረሱ፣
ክምር የሱዳን ወርቅ ገፈራው ነው ለሱ፡፡
ኢትዮጵያ ዛሬ ላይ የወደቀችው ከሀያ ባንክ በላይ ከሚዘርፍ ገዳይ ቡድን ጋር አብሮ ለመስራት በሬ አርዶ ሲታረቅ በሚውል የአፓርታይድ አገዛዝ ላይ ነው። የአገዛዙ ዋና አለማ የኢትዮጵያ አሻራዎችን፣ ታሪካዊ ቦታዎችንና ቅርሳ ቅርሶችን ሁሉ አጥፍቶና ደምስሶ በኦነጋውያን ዝባዝንኬ መተካት ነው። ለዚህ ነውረኛ አገዛዝ ማንኛውንም የኢትዮጽያን ቅርስ ጠብቆ ብሎ አሳልፎ መስጠት እንዲያጠፋውና እንዲያወድመው ማመቻቸት ነው።