ወጣት ፀሐፊያንን በማበረታታት ፅሑፋቸው ለሕትመት እንዲበቃ በማድረግ አስመርቋል:: በአጠቃላይ 3555 የግጥም አንባብያንን አስደምጧል:: ከ50 በላይ ዕውቅ ተዋንያን በድርጅቱ ምርጥ ተውኔቶች የተሳተፉ ሲሆን በሄደበት አካባቢ ሁሉ ሙያዊ ሥልጠና በመስጠት 103 አማተር ተዋንያንን በመድረክ አሳትፏል:: 271 የቴአትር ጉዞዎችን ያደረገ ሲሆን 378 ትርኢቶችን ለተመልካች አቅርቧል:: በየዓመቱ ህዳር ወር ነፃ የሙያ ሥልጠና በትወና – በፅሑፍ -በዝግጅት- በሲንማ ጥበብ በጋዜጠኝነት ወዘተ ከመስጠቱም ባሻገር በዕውቅ የዩኒቨርሲቲ ምሁራን በተለያዩ የትምህርት ዘርፎች ዘውትር አርብና ቅዳሜ ነፃ Tutering በመስጠት ወጣቶችን ይረዳል :: የመጀመሪያውን የአማርኛ ቤተመፃህፍ ከፍቶ የአማርኛ መፃሕፍትን ለሚፈልጉ አገልግሎትይሰጣል:: በአሁኑ ጊዜ ጣይቱ ማዕከል ከኢትዮጵያውያን አልፎ የአፍሪካውያን መሰባሰቢያና ኩራት ነው::
እጅግ የሚያኮራና የሚያስደንቅ ክንውኖችን ያስመዘገበው ድርጅት 19 ነኛ ዓመቱን September 22nd, 6:30 at Civic Building, Silver Spring MD አብራችሁት እንድታከብሩ ይጋብዛል::