>

ኢትዮጵያዊ በየትኛውም አጀንዳ ጊዜ ሊሰጥህና ሊታገስህ ይችላል፤ በእምነቱ ከመጣህበት ግን...!!! (መምህር ታየ ቦጋለ አረጋ)

ኢትዮጵያዊ በየትኛውም አጀንዳ ጊዜ ሊሰጥህና ሊታገስህ ይችላል፤ በእምነቱ ከመጣህበት ግን…!!!!
መምህር ታዬ ቦጋለ አረጋ
በኢትዮጵያ በአጠቃላይና በተዋህዶ ሀይማኖት በተለይ መጠነ ሰፊ ዘመቻ ሲከፈት ይህ የመጀመሪያው አይደለም። መለስ ዜናዊና ታጋይ ጳውሎስ ከዋልድባ ገዳም ጀምሮ በሠሩት ሴራ – በፍጥነት ተጠርተው ጉዳያቸው በሰማይ ችሎት ዕየታየ ነው።
*
ጓድ በላይ፦ የኦህዴድ የፓርላማ ተወካይ፣ የኦሮሚያ ዕንባ ጠባቂ ተቋም አመራር ከመሆኑም ሌላ – በኦሮማራና መላው ኢትዮጵያ ትግል ወቅት በተደጋጋሚ ሳይጠራ እየጠየቀ ጭምር – ከእኛ ጋር በአንድ ለእናቱ Think tank ቡድን ይሰበሰብ ነበር።
ከዚህ በተጨማሪም በዋቄፈና/ኢሬቻ በዓል ላይ ዋና አጋፋሪ ከመሆኑ ሌላ – ከእኔ ጋር በግል በበርካታ ርዕሰ ጉዳዮች ተወያይተን እናውቃለን። የለየለት ካድሬና ለእምነት ቁብ የማይሰጠው ግለሰብ ሲሆን – የግል አቋሙና መሻቱ ብዙም መነሻዬ አይደለምና ልለፈው።
*
ጓድ በላይ ፓትርያርክ ጳጳስ ኤጲስ ቆጶስ – ሌላው ቀርቶ ቆሞስ ደረጃ ላይ የማይገኝ – ተራ ቄስ ነው። ከሲኖዶስ ውሳኔ ውጭ የትም መድረስ አይችልም። አንድ አማራጭ ብቻ አለው – እንደ ተሀድሶዎች የራሱ ኑፋቄ ይዞ – የግል እምነት ማቋቋም።
*
መጯጯህ ሳያስፈልግ ኦሮሚያ ውስጥ ልክ እንደ ትግራይ አማራ እና ሌሎች ክልሎች – ዜማዎችና ቅዳሴዎች በግእዝ – ስብከት በአማርኛና በኦሮምኛ እየሄደ ነው።
የአጀንዳው ባለቤት ሃጂ ጃዋር መሀመድ እንደመሆናቸው – በማይመለከታቸው ገብተው ባይፈተፍቱ እየመከርን – ሙስሊም ቤተሰቦቻችን ዘንድ ሄደው አረብኛ ቀርቶ መስጊድ በኦሮምኛ ይሁን እንደማይሉ ሁሉ – እጃቸውን ከእናት ቤተክርስቲያን እንዲያነሱ እየጠየቅን – በእሳት መጫወታቸው እንደሌላው አጀንዳ ሳይለበልባቸው እንደማይመለስ ልንመክራቸው እንወዳለን።
ኢትዮጵያዊ በየትኛውም አጀንዳ ጊዜ ሊሰጥህና ሊታገስህ ይችላል። በእምነቱ ከመጣህበት ግን – አንዴ ከመቁረጥህ በፊት አስር ጊዜ ለካ። መከላከያውና የፀጥታ ኃይሉ ጭምር በእምነቱ አይደራደርም። ‘ዓሳ ጎርጓሪ ዘንዶ ያወጣል’ እንዳይሆን። ምእመኑ እንኳን ስብከትና አምልኮ ሌላውንም በምክክር ማድረግ ይችልበታል። አትሸቅጡ!
Filed in: Amharic