–ከሁሉም የሚበልጠዉን ኢትዮጵያዊ ማንነት በምልዓት መላበሱ ቢኖር እንዲህ የተምታታ የማንነት ጥያቄ ዉስጥ ባልተገባ ነበር!
1. “የኢትዮጵያ ህዝብ ብዙም እርስ በርሱ አልተቀላቀለም::አልፎ አልፎ መቀላቀል ያለዉ በከተሞች ነዉ:: በመሆኑም ከአማራ እና ከሌላ ብሄር በከተማ የተወለዱ እና አማርኛ ቋንቋ የሚችሉ ሰዎች ሁሉ አማራ ይሁኑ::አማራ ብሄረተኝነቱን ማምጣት የሚችለዉ ኢትዮጵያ ከሚባለዉ ሀገር ማዕቀፍ እራሱን ሲያወጣ ነዉ::ኢትዮጵያ በወረራ እና በቅኝ ግዛት የተፈጠረ ሀገር ነዉ::አማራዉ ሌሎች ነገዶችን ወሮ ኢትዮጵያ የሚባል ሀገር በመፍጠሩ ስህተት ሰርቷል::የአማራ ብሄርተኝነትን ያኮላሸዉ የኢትዮጵያ መፈጠር ነዉ::ኢትዮጵያ የመቶ አመት ታሪክ ያለዉ ሀገር ስለሆነ ቢፈርስ ሁሉም ነገድ የየራሱን ክልል ይዞ መሄድ ይችላል::
አማራም የራሱን ክልል ይዞ ቢሄድ የአማራ ብሄረተኝነት በደንብ ያብባል::እኔም አማራ ነኝ እና የአማራዉ ህልዉና ስለሚያሳስበኝ አማራ ከዬት ወዴት የሚለዉን መጽሃፍ ለመጻፍ ተነሳሁ::” አቶ አንዳርጋቸዉ አማራ ከዬት ወዴት በሚለዉ መጽሃፉ የተረተዉ ነዉ::አቶ አንዳርጋቸዉ ይሄን መጽሃፉን የጻፈዉ የወያኔ/ኢህአዴግ የአዲስ ከተማ ጽ/ቤት አፈ ጉባኤ በነበረበት ጊዜ ከስልጣኑ ተባሮ ባሉት ጥቂት ወራት ዉስጥ ነዉ::የዚህ ጽሁፍ ዋና ፍሬ ሀሳብም የወያኔ የፕሮፖጋንዳ ሰለባ ከሆነዉ ከአንዳርጋቸዉ አ ዕምሮ የፈለቀ የተኮረጀ ሀሳብ መሆኑን መጽሃፉን እንደዋጣ በግል ጋዜጦች ላይ መጽሃፉን ተችቼ ሀሳቤን ሰንዝሬ ነበር:: አንዳንድ ሰዎች ግን አማራ የሚባለዉ ቃል ስለተጠራላቸዉ አንዳርጋቸዉ ጽጌ የአማራ ጠበቃ ነዉ እያሉ እንብር እንብር ሲሉ እንደነበረም አስታዉሳለሁ::እረ አሁን ድረስ የሚሉም ነበሩ::
2. የአንዳርጋቸዉ ጽጌ ሁለተኛ መጽሃፉ “ነጻነት እማያዉቅ ነጻ አዉጭ የሚል ነዉ::በዚህኛዉ መጽሃፉ ከአማራ እና ኦሮሞ ነገድ እንደሚወለድ አብራርቶ ጽፏል:: ይሄ መጽሃፉ ከወያኔ ተጽኖ በተወሰነ ደረጃ የተላቀቀበት ወቅት እና ወደ ቅንጅት አስተሳሰብ ያዘነበለበት ወቅት ላይ ስለነበረ መላክም ሀሳቦችን ይዟል ማለት ይቻላል::አንዳንድ ትንታኔዎቹም ጠንካራ የሚባሉ ናቸዉ::የሚያሳዝነዉ ግን የዚህ መጽሃፍ መቋጫም የሚደመደመዉ የተዋህዶን ሀይማኖት በመሳደብ እና ተዋህዶን ደናቁርት አቢዮተኞች ላጠፉት ጥፋት ሁሉ ተጠያቂ በማድረግ ነዉ::ይሄ የድንዛዜ አካሄድ በአብዛኞቹ የዚያ ትዉልድ ፖለቲከኞች እራሳቸዉን እንዳዋቂ ለማሳያነት የሚተቀሙበት ስልት ነው::
የእግዚአብሄርን ቤት በመሳደብ እራስን አዋቂ ማድረግ ትልቁ ስልታቸዉ ነዉ::እናም አንዳርጋቸዉም ነጻነት የማያዉቅ ነጻዉጭ በሚለዉ መጽሃፉም ተዋህዶን አርክሶ እና ኮንኑ የትንታኔዉ መቋጫ አድርጓታል:: በእሱ ትንታኔ መሰረትም ዲሞክራሲ በኢትዮጵያ እንዳያብብ ትልቅ እንቅፋት የሆነዉ የቤተክህነት ባህል እና ስነልቦና ነዉ::ከአቢዮታዉያኑ ኢ አማኞች ጋር ቤተክህነትን በምን ገመድ ጎትቶ እንዳገናኛት ግን ሳይገልጽልን አልፎታል::
አስቂኙ ነገር ታዲያ አንድ የተዋህዶ ሰባኪ ነኝ የሚል ወዳጄ የአንዳርጋቸዉን መጽሃፍ አነበብኩት ብሎ ማብራሪያ ሰጠኝ::ተዋህዶ ላይ ያለዉን እይታ እንዴት አገኘህዉ ብለዉ “መቼም ግሩም ገልጾታል” ብሎኝ ቁጭ::ይሄ ሰባኪ ነኝ ባይ መጽሃፉን እንዳላነበበዉ ወይም መጽሃፍ አንብቦ እንደማይረዳ ሲገባኝ ከትከት ብዬ ስቄቤት እንደነበረ ትዝ ይለኛል::ለምን ትስቃለህ ቢለኝ “መቼም እናንተ ዲያቢሎስ ቢሰድባችሁ አትቆጡም::የክርስቶስን ቤት የሚሳደብን ሁሉ ታደንቃላችሁ አይደል?” ብዬ ብለዉ የመለሰለኝ መልስ እስካሁን ያስቀኛል::”እንዴ ? አንዳርጋቸዉ ተዋህዶን ሰደበ እንዴ?” ብሎኝ ቁጭ::በቁጥሩ ቀላል የማይባል ሰዉ እንዲህ ይመስለኛል::ነገር ከመመርመር ጩህት እደመቀበት እሚረግሙት ዳስ ዉስጥ ገብቶ ከበሮ የሚደልቅ::
3. አንዳርጋቸዉ አሁንም ሶስተኛ መጽሃፉን አሳትሟል:: ይሄ መጽሃፉ ደግሞ በተለዬ ሁኔታ ዉስጥ ሆኖ የጻፈዉ ይመስላል::በአንድ መልኩ እስር ቤት እያለ የጻፈዉ ታሪክ እና ከ እስር ቤት ከወጣም ብኋላ አሁን በኦነጋዉያን ተጽዕኖ ዉስጥ ወድቆ የጻፈዉ መጽሃፍ የቀደሙትን የራሱን ትርክቶች ደምስሷቸዋል:: ዋናዉ ማንነቴ ነዉ ሲል አማራ ከዬት ወዴት በሚለዉ መጽሃፉ ያተተዉንም ፍልስፍናዉን እና ማንነቱንም ፍቆ በመጣል አማራ የሚባል ህዝብ የለም::እኔም ኦሮሞ ነኝ ብሎ ቁጭ ብሏል::እኔ ኦሮሞ ነኝ ማለቱ አንዳች ክፋት የለዉም::አስገራሚዉ ነገር ከኔ በላይ አማራ የለም ሲል አማራ ከዬት ወዴት በሚለዉ መጽሃፉ የተረከዉን ማንነቱን በመፋቅ እንዴዉም አማራ የሚባል ህዝብ የለም ማለቱ ነዉ ነዉ::
—
ከላይ የተነሱ ሶስት የሰነልቦና ቀዉሶችን እንዉሰድ እና አላማቸዉ ምን እንደሆነ እንይ
—
1.አማራ ከዬት ወዴት የሚለዉ መጽሃፍ የተጻፈዉ እኔም አማራ ነኝ::አማራን ወክዬ ስልጣን እይዛለሁ የሚል ትልምን ተንተርሶ ነዉ::ይሄ ሀሳብ አይከፋም ነበር::ክፋቱ ግን አማራ ያልሆኑ የከተማ ሰዎችን ሁሉ አማርኛ ስለሚናገሩ ብቻ አማራ ይሁኑ::ኢትዮጵያም ትፍረስ::ኢትዮጵያ ስትፈርስ የአማራ ብሄረተኝነት ይቀጣጠላ የሚለዉ ሸዉራራ ሀገር አፍራሽ ህሳቤ ነበር::የዚህ ሸዉራራ ህሳቤ መነሻዉም ከአማራ በላይ አማራ ሆኖ ለመገኘት የታቀደ መሰረት የሌለዉ ስሁት ስነልቦናዊ ቀመር ነበር::
2. በሁለተኛዉ መጽሃፉ ደግሞ ኦሮሞነቱን እና አማራነቱን ለማሳዬት ከሁለቱ ነገዶች መወለዱን ለማታቀስ የተገደደበት ሁኔታ ነበር::ይሄዉም ቅንጅት ህብረ ብሄራዊነትን እያገነነዉ ስለመጣ ነበር::በዚህ ህብረ ብሄራዊነት ምህዳር ዉስጥ በሁለቱ ትልልቅ ነገዶች ተወክሎ መሪነቱን ለመጨበት እና ከኔ በላይ ወካይ የለም የሚል ታሳቢን ያነገበ ነዉ::
3. አሁን ነገሮች ሲገለባበጡ እና የኦሮሞ ብሄረተኝነት ጉልበት ሲያገኝ ደግሞ ሌላ የስልታን ጎዳና ስልጥ መቀዬስ አስፈላጊ ሆነ::እኔ ኦሮሞ ነኝ::አማራ የሚባል ነገድ የለም ብሎ ቁጭ::ይሄንንም በማለት አሁንም በስልጣን ወንበር ስር የማድፈጥ ስትራቴጅ ስልት እንጅ የኦሮሞን ህዝብ በተለዬ የመዉደድ ባህሪ ኖሮት አይደለም::የስልታን መንገዱ እጅግ ዘወርዋራ እና ብዙ መሆኑን አልሞ የተነሳዉ አንዳርጋቸዉ ጽጌ ሁሉንም ስልቶች እየቀያዬር እየሞከራቸዉ ይመስላል:: ሁሉም የከተማ ሰዎች እና የአማራ ክልል ህዝብ አማራ ይሁን ሲል አማራ ከዬት ወዴት በሚለዉ መጽሃፉ ያወጀዉ አንዳርጋቸዉ ጽጌ አሁን ደግሞ አማራ የሚባል ህዝብ የለም ብሎ እርፍ::
አንዳርጋቸዉ ጽጌ እና ግንቦት ሰባት በዚሁ አጋጣሚ የከረረ ጸብ ዉስጥ የገቡትን የአማራ ብሄረተኛ ሀይል የመበቀያ ስልትም ያገኙ መስሏቸዉ ሊሆን ይችላል አማራ የለም የሚለዉን ትርክት ይዘዉ የመጡት::አማራ የለም ካልን የአማራ ብሄረተኝነት ይዳከማ ብለዉ አስበዉ መሆኑ ነዉ::
የሽህ እና ህሽ አመታት የአማራ ታሪክን ካለማወቅ የሚመነጭ ሸዉራራ ህሳቤ እና ፈጥኖ ደራሽ ሀሳብ ሁሌም ስሁት ነዉ::የአማራ ህዝብ እንዲህ በቀላሉ የሚፈረካክሰስ ህዝብ አይደለም::የአማራ ህዝብ ሰላም እና እረፍት እስካላገኘ ድረስም የአማራ ወጣቶች እንደ አማራ ብሄረተኛ ወይም እንደ ኢትዮጵያ ብሄረተኛ ወይም በሌላ መልክ ሆነዉ ትግል ከማድረግ አይቆሙም::ስለዚህ መፍትሄዉ የችግሩን ስር ማድረቅ እንጅ ሀሰተኛ ትርክ መፍጠር አልነበረም::
———————
የመደምደሚያ ምክር ለአንዳርጋቸዉ ጽጌ
—————–
ከሁሉም የሚበልጠዉን ኢትዮጵያዊ ማንነት በምልዓት ብትለብሰዉ እንዲህ የስነልቦና ቀዉስ ዉስጥ አትገባም ነበር::የኢትዮጵያም ስልጣን እግዚአብሄር ከፈቀደልህ ያንተ ይሆን ነበር::ስልጣን ከእግዚአብሄር እንጂ ከዘርህ ወይም ከፓርቲህ አይመነጭም::ሃሃሃሃ…ለኮሚኒስቶች የሚያስቅ የካህን-ንጉስ ፍልስፍና ነገርኩህ አይደለም?
ለማንኛዉም ኢትዮጵያዊነት ከሁሉም ማንነቶች በላይ መሆኑን ብታዉቅ: አንተም ከሁለቱ ነገዶችም ተወልደህ ቢሆን: ወይም ከኦሮሞ ብሄር ብቻ ተወልደህ ቢሆን: ወይም ቀድሞ አማራ ነኝ እንዳልከዉ ከአማራ ብሄርም ተወልደህ ቢሆን ከንኡስ ማንነትህ የሚበልጠዉ አምንነት ኢትዮጵያዊ ማንነት ነዉ ነዉ::ከአማራነትም: ከኦሮሞነትም የሚበልጠዉን ኢትዮጵያዊ ማንነት በእምነት ብትለብሰዉ ከሁሉም በላይ ትከብር ነበር::
እንዲህ አንዴ አንዱ የነገድ ማንነትህ ትዝ ሲልህ ሌላ ጊዜ እንደሌለ ሲጠፋብህ: ሌላ ጊዜ ከሁለት መወለድህ ሲታሰብህ ባትተህ እና ዋትተህ መመላለስህ ያሳዝናል::እንደ ኢትዮጵያዊ ወንድሜ ብቻ ሳይሆን እንደ አንድ የአዳም ልጅ ወንድሜ የማንነትህ ነገር እንዲህ እስከ አንጥንትህ ድረስ ለምን እንደ በላህ ሳስበዉ አሳዘንከኝ::
የሆኖ ሆኖ ተለይቶ የዘር ማጥፋት እየተደረገበት ያለበትን የአማራ ነገድ የለም ስላልክ የምታተርፈዉ የፖለቲካ ትርፍህን አንተዉ ታጭደዋለህ::የአማራ ነገድ በዚህ ወቅት የለም የሚለዉ ሰዉ ሳይሆን የሚፈልገዉ አማራን ለይታችሁ አታጥቁ:ፍትህ አድርጉ:ሁሉንም ኢትዮጵያዉያን እኩል የሚያደርግ ሀገር ፍጠሩ:ሁሉንም ነገዶች እኩል የሚያስተናግድ ፍጠሩ የሚል ኢትዮጵያዊ ፖለቲከኛ ነበር የሚፈልገዉ::
ለማኛዉም ኢትዮጵያዊነትን መቶ አመት ነዉ እድሜዉ ብለህ በቅኝ ግዛት የተፈጠረ ሀገር ነዉ ብለህ ብትክደዉም መጽሃፍ ቅዱስ ግን የሚተርክልን ኢትዮጵያዊ ማንነት ከማንኛዉም የነገድ ማንነት በላይ መሆኑን ነዉ::በመጽሃፍ ቅዱስ እግዚአብሄር እራሱ ኢትዮጵያዊ ልጄ ነዉ ብሎ መስክሯል እና::
ኢትዮጵያዊነትን ለኢትዮጵያዊ ሁሉ የሰጠዉ እራሱ እግዚአብሄር ነዉና::የሚቀበለዉ ኢትዮጵያዊ መልካም አደረግ::የማይቀበለዉም ኢትዮጵያዊ መብቱ ነዉ:: ከእዉነቱ ስትቆረጥ ይዘህዉ የምትመጣዉ ትንታኔ ሁሉ ሀስት እና እርስ በርሱ የሚምታት ነዉ::አንዴ አማራ ነኝ: አንዴ አማራ እና ኦሮሞ ነኝ: አንዴ አማራ የሚባል ህዝብ የለም እያልክ መከራህን ታያለህ::አንዴ በስልታን ጥም: አንዴ በበቀል: አንዴም በግል ተራ ፍልስፍና ስትዋልል ትዉላለህ::
ኢትዮጵያዊነት ተፈልጎም የማይገኝ ማንነት ነዉ::ኢትዮጵያዊ ነኝ የሚለዉ ህዝብ እንኳን ቢጥለዉ ሌላ ወገን ያነሳዋል::ጥቁሩ አለም የነጻነት: የእኩልነት: በእግዚአብሄር መንፈስ መወደድን እና በ እግዚአብሄር አይን የታወቀ ህዝብ መሆኑን ማረጋገጫ ቢፈልግ የሚያገኘዉ ኢትዮጵያን እና ኢትዮጵያዊነትን ነዉ::
ስለዚህ ዛሬ ኢትዮጵያ የተባለዉ ህዝብ ኢትዮጵያዊነትን አዉልቆ ቢጥለዉ ሌላዉ ወገን አንስቶ ይልብሰዋል::
ኢትዮጵያ ጥሎባት እናንተ ከወያኔ ጋር ሆናችሁ በቀየሳችሁት የነገድ ፖለቲካ ስር ገብታለች እና ገና ብዙ በርካታ ዉጥንቅጦች እና የማምንነት ቀዉሶችን የተሸከሙ ዜጎች ታስተናግዳለች:: አንዴ ይሄኛዉን ነኝ::ሌላ ጊዜ ያኛዉን ነኝ የሚሉ የማንነት ቀዉስ ዉስጥ የሚዳክሩ በርካታ ዜጎች የሚተራመሱባት ሀገር::
በነገራችን ላይ ኢሳያስ አፈወርቂ በአንድ ወገን ኢትዮጵያዊ ማንነቱን ጥሎ ነዉ ኤርትራዉያንን ከወንድሞቻቸዉ ኢትዮጵያዉያንን የነጣጠላቸዉ::መለስ ዜናዊም በአንድ ወገን ኤርትራዊ ማንነቱን ክዶ ነዉ ኢትዮጵያዉያንን ከወንድሞቻቸዉ ኤርትራዉያንን የነጣጠሏቸዉ::ይሄም ሁሉ የክፋት እና ስልጣን መያዝን እንደ ግብ የመዉሰድ የተሳሳተ ፍልስፍና ነዉ::
የሆነ ሆኖ እግዚአብሄር የታመነ ነዉና ህዝቤ ያለዉን እና የተወደደ ኢትዮጵያዊነት የተላበሰዉን ህዝቡን ያድናል::