ቬሮኒካ መላኩ
<< ሰልፉ ሌብነት ስራ ስለሆነ ልጆቻችን ነፃ ይውጡልን ፣ ሌብነት ይፈቀድልን ” የሚል በመሆኑ ግራ የሚያጋባው ኢትዮጵያውያንን ብቻ ሳይሆን አለምንም ጭምር ነው። ለነገሩ ” እስካልተያዝክ ድረስ ሌብነት ጥሩ ስራ ነው ” በማለት ለመጀመሪያ ጊዜ በአገሪቱ ፓርላማ የተናገረው የቀድሞው ጠ/ሚራቸው መለስ ዜናዊ ነው!!
በ130 አመታት የኢትዮጵያ ታሪክ ” ሌብነት ይፈቀድ ” በማለት ሰላማዊ ሰልፍ የመውጣት ታሪክ ይሄ ሁለተኛው ነው።
…
እውቁ የታሪክ ባለሙያ ተክለፃድቅ መኩሪያ መዝግበው እንዳለፉት
አፄ ቴዎድሮስ ወደ ስልጣን እንደመጣ የመጀመሪያ አዋጁ << ሁሉም በሙያው ይሰማራ ፣ ገበሬም ወደ እርሻህ ግባ ፣ ነጋዴም ንግድህን አጧጡፍ ፣ የቀረውም ሰው ወደየስራው አንድመለስ ታውጇል ” በማለት አዋጅ ያስነግራሉ።
…
በዚህ ጊዜ ተከዜን ተሻግረው ደብረታቦር ከተማ የመጡ ጥቂት ሰዎች ወደ አፄ ቴዎድሮስ በቀጥታ ሰልፍ አደግድገው በመግባት << ጃንሆይ ሰውን ሁሉ በየስራህ ግባ ካሉት እኛም ከሌብነትና ከሽፍትነት በቀር ሌላ ስራ የለንምና ይህንኑ ይፍቀዱልን> > ሲሉ አመለከቷቸው።
…
አፄ ቴዎድሮስም ለሰልፈኞቹ << እኔም ለራሴ ታማኝ ዘበኛ ለመቅጠር የእናንተ አይነት ልማድ ያለው ጠንካራ ሰው ስለምፈልግ ሌላ ባእድ ሳትጨምሩ የእናንተ አይነት ስራ የሚሰሩትን ሰብስባችሁ ይዛችሁ ኑ ” በማለት በቀጠሮ ያሰናብቷቸዋል። በቀጠሮውም ቀን ሌቦቹ ተሰብስበው ሲመጡ አፄ ቴዎድሮስ አንድ እጃቸው ላይ ፈረዱባቸው ከዛን ጊዜ በኋላ ሌብነት ለብዙ አመታት በኢትዮጵያ ጠፍቶ በሰላም ህዝቡ መኖር ጀመረ ።>> በማለት እውቁ ምሁር ተክለፃድቅ መኩሪያ “አፄ ቴዎድሮስ ” በሚለው መፅሃፉ ገፅ 193 ላይ ፅፏል።
…
ጠቅላይ ሚኒስትር አቢይ አህመድ እጅግ ሩህሩህ በመሆኑ እንጅ መርከብና አውሮፕላን የሰረቀ ሌባ እንደ ቴዎድሮስ መረር ያለ ቅጣት ቢቀጣ ኖሮ የዛሬውን የድፍረት “ሌባ ይለቀቅልኝ የሚል ሰልፍ ባልተመለከትን ነበር።
…
ሙሰኛ በየትም አገር ቅጣቱ ከባድ ነው ። በቻይና እንኳን መርከብ ይቅርና የህዝብ የሆነን መቶ ብር የሰረቀ በስቅላት አንጠልጥለው ይቀጡታል ። በአረብ አገሮች ሌባ እጁ ይቆረጣል ፣በአውሮፓና አሜሪካ በስልጣን ላይ ሆኖ የህዝብ ንብረት የሰረቀ እስከ እድሜ ልክ እስራት ይጠብቀዋል። ከአፍሪካ ውጭ ሌብነት በየትኛውም አገር ፀያፍ ነው። ጆርጅ በርናንድሾው ” There is no little pregnancy ” ( ትንሽ የሚባል እርግዝና የለም) እንዳለው ትንሽና ትልቅ የሚባል ሌባ የለም ። ሁሉም ሌባ ነው ። ሌባ ከአገር እንድጠፋ ከተፈለገ በሰላማዊ ሰልፍ ሌብነትን ማበረታታት ሳይሆን ተገቢውን ቅጣት መስጠት ያስፈልጋል።