>
5:13 pm - Friday April 19, 4211

ሚስጥራዊ ስብሰባው ምን ይዞ ይመጣ ይሆን ?  (ሀብታሙ አያሌው)

ሚስጥራዊ ስብሰባው ምን ይዞ ይመጣ ይሆን ? 
ሀብታሙ አያሌው
ከእለተ አርብ ጀምሮ አዲስ አበባ በመግባት ቅዳሜና እሁድ ሚስጥራዊ ስብሰባ ሲያደርጉ የነበሩት የአፋር ክልል አመራሮች የኢህአዴግ ተወካይ ባለበት በግምገማ ሲጠዛጡዙ ቆይተዋል።
ተገማጋሚዎቹ ከዶክተር አብይ አመራር የተሰጠውን አቅጣጫ በተገቢ መንገድ ከተወጡ የአመራር ለውጥ በማድረግ ( በቅርቡ የኢፌድሪ መከላከያ ሚኒስትር  ) ሆነው የተሾሙትን ወ/ሮ አይሻን ሊቀመንበር አድርገው በመሰየም ያጠናቅቃሉ ተብሎ ይገመታል።  ከውስጥ ምንጭ ያገኘሁት መረጃ እንደሚያሳየው የወ/ሮ አይሻ ባለቤት አቶ አወል ኦርቢስ የትራንስፖርትና መገናኛ ሚኒስትር ዴኤታ ሆነው በመሾም ወደ ሚኒስትሯ ወ/ሮ ዳግማዊት ሞገስ ቢሮ ተልከዋል።
ቀደም ሲል የነበረኝ መረጃ የሚያሳየው ለሊቀመንበርነት የታጨው የክልሉ ም/ሊቀመንበር ሆኖ እየሰራ ያለው አቶ አወል አርብአ እንደነበረ ነው።  አወል አርብአ የተማረ እና በዶክተር አብይ መንግስትም ሆነ  በክልሉ ለውጥ እንዲመጣ እየታገሉ ባሉ ወጣቶች ተቀባይነት ያለው እንደነበረ ነው።  ይሁን እንጂ ከቅርብ ቀናት ወዲህ ከበስተጀርባ  አወል አርብአ አማራ ነው የሚል ቅስቀሳ እንዲከፈትበት መደረጉ ይነገራል።  ይህ ጉዳይ በቸልታ የሚታለፍ ስላልሆነ ሴራው በማን ለምን ተከናወነ ?  የሚለውን ለማጣራት የማደርገው ጥረት የሚቀጥል ይሆናል።
በጥቅሉ ግን የአፋር ክልል ሁኔታ እና ሚስጥራዊ ስብሰባው ከምንም በላይ መቀሌ ላይ ከፍተኛ ድንጋጤና ንዴት ፈጥሯል።  ለውጡን እና የእስር ዘመቻውን እንደግፋለን የሚል መግለጫ ካወጡ ሳምንት ሳይሞላ ሌላ ተቃራኒ መግለጫ ለማውጣት ካስገደዱት ገፊ ምክንያቶች አንዱ ይሄው ጉዳይ ሳይሆን እንዳልቀረ የውስጥ ምንጮች ይገልፃሉ
 
ሰበር ዜና 2
“ለውጡን እንሰብራለን!” የሚል  መረጃም ከወደ ሰሜን ደርሶናል!!!
 የትግራይ ክልል መንግስት በይፋ ተቃውሞውን እና አቋሙን ግልፅ በማድረግ ለውጡን ለመቀልበስ
እንደሚነሳ ማሰታወቁን የትግራይ ማስሚዲያ ዘግቧል።  “የኢትዮጵያ መንግስት በሙስናና የሰብኣዊ መብቶች
 ጥሰት ስም የጀመረው እንቅስቃሴ ኣቅጣጫውን ስቶ የትግራይ ህዝብ ለማንበርከክ የሚደረግ ጥረት ስለሆነ አንቀበለውም። ከዚህ በተጨማሪም የውጭ ጣልቃ ገብነት አለው ብለን እናምናለን። “
Filed in: Amharic