>

ጋዜጠኛ ለታሪክ ጀርባውን ሲሰጥ አስፈሪም አሳፋሪም ይሆናል!!! (አቻምየለህ ታምሩ) 

ጋዜጠኛ ለታሪክ ጀርባውን ሲሰጥ አስፈሪም አሳፋሪም ይሆናል!!!
አቻምየለህ ታምሩ 
* አገራችን ከወይዘሮ  ሣሕለ ወርቅ ዘውዴ በፊት ንግስተ-ነገስታት ዘውዲቱ ምኒልክ፣  ሕንደኬ፣ ማክዳና ዮዲት የሚባሉ ሴት ርዕሳነ ብሔራት ነበሯት!

የኢትዮጵያን እድሜ ከወያኔ የአገዛዝ ዘመን ጀምረው  የሚቆጥሩ እንደ BBC News Amharic አይነት ጋዜጠኞች ወይዘሮ ሣሕለ ወርቅ ዘውዴን የመጀመሪያዋ  ሴት የኢትዮጵያ ርዕሰ ብሔር እያደረጓቸው ይገኛሉ። ከዛሬ 98 ዓመታት በፊት ወይዘሮ ሣሕለ ወርቅ ዘውዴ ዛሬ በገቡበት የኢትዮጵያ ቤተ መንግሥት ውስጥ የኢትዮጵያ መሪ ሆነው  የገቡ ሌላ ሴት ርዕሰ ብሔር ነበሩ። ስማቸው ወይዘሮ ዘውዲቱ ምኒልክ ይባላል!

* ወይዘሮ  ሣሕለ ወርቅ ዘውዴን ርዕሰ ብሔር  አድርጎ የሾመው ኦሮሞው ዐቢይ አሕመድ ነው።  
* ወይዘሮ ዘውዲቱ ምኒልክንም  ርዕሰ ብሔር አድርገው የሾሟቸው የዘመኑ አንጋሽና የጦር መሪ የነበሩት  ኦሮሞው  ፊታውራሪ ኃብተ ጊዮርጊስ ዲኔግዴ (አባ መላ)  ናቸው። 
ከወይዘሮ ዘውዲቱ ምኒልክ በፊት ሕንደኬ፣ ማክዳና ዮዲት የሚባሉ ሴት የኢትዮጵያ ርዕሳነ ብሔራት ነበሩ። ወይዘሮ ዘውዲቱ ምኒልክን  ጨምሮ  ከወይዘሮ ሣሕለ ወርቅ ዘውዴ በፊት የነበሩት የኢትዮጵያ  ሴት  ርዕሳነ  ብሔራት ሁሉ በሥልጣን ረገድ ከዛሬዋ ርዕሰ ብሔር እጅግ  የገዘፈ የሙሉ ሥልጣን ባለቤቶች ነበሩ።
 የዛሬዋ ርዕሰ ብሔር የፖለቲካ ሥልጣናቸው  የይስሙላ ወይንም cermonial ነው። ከወይዘሮ ሣሕለ ወርቅ ዘውዴ በፊት የነበሩት የኢትዮጵያ  ሴት  ርዕሳነ  ብሔራት ግን  ዘውድ እየጫኑ የሚያነሱ፣ ሹም ሽር የሚያደርጉ፣ ጦር የሚያዝዙ፣ ብቸኛ  የአገር መሪዎችና አባወራዎች  ነበሩ! የዛሬዋ ርዕሰ ብሔር  ወይዘሮ ሣሕለ ወርቅ ዘውዴ ግን ሌላው  ቢቀር ከተሰጣቸው ሥልጣን መካከል ዋና  የሆነው  ሕግ የማጽደቅ ሥልጣን እንኳ  ረቂቁ   ቀርቦላቸው በ15 ቀናት ውስጥ ካልፈረሙት  የርሳቸውን ይሁንታ ሳያገኝ ሕግ መሆን የሚችልበት ትርጉም የሌለው ሥልጣን ነው ያላቸው!
Filed in: Amharic