>

ቅቤና ማር ተከራከሩ!!! (ዳንኤል ክብረት)

ቅቤና ማር ተከራከሩ!!!
 ዳንኤል ክብረት
ማርም ተናገረች፡-“የምጣፍጠው እኔ አናት ላይ የምትወጭው ግን  አንቺ ነሽ ለምነድነው? አለቻት።
ቅቤም ፡-“እኔም ወድጄ አይደለም ገፍተው፣ ገፍተው ነው አናት ላይ ያወጡኝ” አለች ይባላል።
ቅቤ ቅቤ የሚሆነው ተንጦ፣ተንጦ ነው። እግዚአብሄር ሁሉም ሎሌው ነው። በክፉዎች ሳይቀር ይሰራል።
ወዳሰበልን  የሚያደርሰን እየገፉን ነው።
ካልተገፋን ያለንበትን ትንሽ ቦታ ተላምደን እንኖራለን።እርሱ  በደጎች አይገፋንም ፣ደጎች መግፋት ባህሪያቸው አይደለምና። ክፉዎች ግን ቅድስናም ይሉኝታም የላቸውምና በነርሱ ይገፉናል።
 እነርሱ የሚያውቁት ወደ ገደል እንደሚገፉን ነው፣ሳያውቁት ግን ወደ ተራራ ይገፉናል።
ጠላቶች የነጻ ሰረገላ ናቸው ።ለኛ ከ ማይገባን ቦታ እየገፉን ወደ ሚገባን ቦታ…ከዝቅተኛ ወደ ከፍተኛ ቦታ ያደርሱናል።
 በእውነት ጌታ ሆይ ጠላቶቻችንን ባርክልን። እነርሱ ባይኖሩ ስራው አይበዛልንም ነበር።
 ይህን ጥንቁቁ ሕይወት፣ይህን ዝግጅት፣ይህን ቶሎ ቶሎ መስራት ያገኘነው ከጠላቶቻችን ነው።
እያንዳንዱን ቀን  በትክል እንድንኖር ያተጉንን  ጠላቶች  እባክህ ባርክልን። የሰአት ደወል ብንሞላ ጠዋት 12 ሰዓት ሞልተነው፣ማታ 12 ሰዓት ሊጮህ ይችላል።
ቀስቅሱን ብንላቸው ወዳጆቻችን ከስራችን ለእንቅልፋችን አዝነው ይተውናል። ክፉዎቹ ግን በሰአቱ ያነቁናል ።እንደነዚህ ያሉ ነጻ ደዎሎችን ያስቀመጠልን አምላክ ስሙ ይባረክ።
እነርሱ እንዳይነቅፉን ስንጠነቀቅ የቅድስናን  ሕይዎት ያለማምዱናልና እነዚህ ጠባቂዎቻችን ናቸው።
የተገፉ ሁሉ  ከፍ እንጂ ዝቅ ሲሉ አይተን አናቅም። ገፊዎች ሲገፉን ከእኛ የክፋት ሰፈር ምን ትሰራላችሁ? እልፍ በሉ እያሉን ነው።
ጠላቶች ሀሰተኛ ወዳጆችን ወስደው እወነተኛ ወዳጆችን ያስቀሩልናል።ክፉዎች ጥሩ ማጣሪያ ናቸው።ተረስተን የምንኖረውን  እነርሱ ያሳውቁናል።በነጻ ማስታወቂያ ይሰሩልናል።
ሰዎች ስማችንን የሚያነሱት በሁለት ነገር ነው።
ስለሚወዱንና ስላስደሰትናቸው ሲሆን በተቃራኒው ደግሞ ስለሚጠሉንና ስላስጨነቅናቸው ነው።
እንዲሁ ርእስ መሆን አይገኝም። የአትርሱኝ ሳንከፍል ላስታዎሱን በረከት ይሁን ዮሴፍ ባይገፋ ኖሮ ጎበዝ እረኛ ሆኖ ይቀር ነበር።
በመገፋቱ የግብጽ ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነ።ጠላት ያውቃል እንላለን፣እንደ ጠላት ግን አላዋቂ የለም። ኢየሱስን ከኢየሩሳሌም ሊያጠፉ ገደለው ፣በሞቱ ግን በአለም ሁሉ አበራ። ጠላት ሰፈር እየቀማ ዓለም ያወርሳል።
ሰው ማፍረስ ይችል ይሆናል፣እግዚአብሄር ደግሞ ማስነሳት ይችላል/ዮሐ• 2 ፡ 19/።
Filed in: Amharic