“ወያኔ የዘር ፖለቲካን በአግባቡ ተጠቅሞ ከራሳችን አብራክ የወጡ እበላ ባዮችን በመሾም ለሃያ ሰባት አመት ጋጠን ቦጠቦጠን አዳከመን!! ኢትዮጵያዊነት ሲፋፋ ወያኔ ይደክማል ፤ ኢትዮጵያዊነት ሲዳከም ግን ወያኔ አፈር ልሶም ቢሆን ዳግም ይነሳል!!
ስለአማራ ህዝብ መብት ለመታገል አማራ መሆን አይጠበቅም ህሊና ያለው ኢትዮጵያዊ መሆን ይበቃል !!”
ፕ/ር ብርሀኑ ነጋ ~ ባህርዳር ለተሰበሰበው ህዝብ ።
የባህርዳሩ የአግ7 አቀባበል ድንቅ ኢትዮጵያዊነት የታየበት ነበር። ዶ/ር ብርሀኑ ነጋ እና አንዳርጋቸው ጽጌ ከአማራ መገናኛ ብዙሀን ጋር ቀጠሮ ይዘዋል። የአግ7 የአጭር ጊዜና ዘለቄታዊው ትልም ይተነተናል።
የኢትዮጵያዊነት ሞተ ፣ አበቃለት ሲባል የሰሞኑ ቀናት ሟርቱ የውሸት እንደሆነ አሳይቶናል። ገና ጎንደር ይቀጣላ የአባጃሌው ሀገር !
አማራ በኢትዮጵያዊነቱ ሳይደራደር ባለሙሉ መብት ዜግነቱንና ነጻነቱን ያውጃል !