>

የኛ ትውልድ ውቃቤ ርቆታል (ፕሮፌሰር ሃይሌ ገሪማ)

”የኛ ትውልድ ውቃቤ ርቆታል”
ፕሮፌሰር ሃይሌ ገሪማ
     በባለፈው ዶክተር ነጋሶ ጊዳዳ በኦህዴድ ሲሸለሙ እኔ የተሰጠኝ ያህል ነበር ደስ ያለኝ።እናም እታች ያለችውን ቪዲዮ አያይዤ ደስታየን ገለጽኩ።
 * ይህንን ያረኩት ከኢህአዴግ ጋር ሆነው ስላልበደሉኝ አይደለም።
 * ወይም ከመጀመሪያው የህወሃት ህገ መንግስት ሲወጣ   አብረው ስላላጸደቁም አይደለም ።
* ከህወሀት በላይ ህወሀት ሆነው ሲያቆስሉን እንደነበሩም ዘንግቼ አይደለም።
በቃ ሰው ይሳሳታል ከስህተቱ ደግሞ ተምሮ ፓርላማን ረግጦ እስከወጣ ይቅር ይባላልና ይህንን በማሰብ እኔም ክብር ሰጠሁ።
 ይሄው አክብሮቴ ሳይጎልባቸው /ሳናጎልባቸው /ጭራሽ ኮከባማ ባንዲራ ስላልያዛችሁ ህግ ጥሳችኋል ይሉናል።ያወጡት ህግ ለራሳቸው  ሳይበጃቸው።
ሁኔታቸው ግን ይህን የፕሮፌሰሩን  “ውቃቤ የራቀው ትውልድ” ነበር እንዴ እንድል አስደፍሮኛል።
Filed in: Amharic