>
5:13 pm - Thursday April 18, 8768

የኢትዮጵያና የኤርትራ ህዝቦች የህዝብ ለህዝብ ግንኙነት በመጀመር ወንድማማችነታቸውን ያረጋግጣሉ!!! [የትግራይ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት መግለጫ]

የኢትዮጵያና የኤርትራ ህዝቦች የህዝብ ለህዝብ ግንኙነት በመጀመር ወንድማማችነታቸውን ያረጋግጣሉ!!!
የትግራይ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት መግለጫ
በኢትዮጵያ እና በኤርትራ መካከል ለ20 ዓመታት የዘለቀው ሰላምም ጦርነትም የሌለበት ሁኔታ በዘላቂነት ለመፍታት በኢህአዴግ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ የቀረበውን ወሳነ ተከትሎ ህወሓትና የትግራይ ክልል መንግስትም በተመሳሳይ አኳኋን የትግራይ እና የኤርትራ ህዝቦች ወንድማማችነት ወደነበረበት ሁኔታ ለመመለስ ጠንክረው እንደሚሰሩ መወሰናቸውንና ውሳኔያቸውም ለመላው የትግራይ ህዝብ፣ ለሁሉም የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች እንዲሁም ለኤርትራ ህዝብ ይፋ ማድረጋቸው የሚታወቅ ነው፡፡
የትግራይ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የኢትዮጵያ እና የኤርትራ መንግስታት የሁለቱ ህዝቦች ሰላም በዘላቂነት ለመፍታት እያሳዩት ያለ ዝግጁነትና ተነሳሽነት ያደንቃል፡፡ በተለይ የኤርትራ ህዝብ ለ20 ዓመታት የዘለቀውን ሁኔታ በመፍታት የኢትዮ-ኤርትራ ወንድማማችንትና ወዳጅነት ለማጠናከር ያሳየው ፍላጎት፣ ጉጉትና ፍቅር እጅግ የሚያስደስትና ከፊት ለፊታችን ብሩህ ተስፋ እንዳለም የሚገልፅ ነው፡፡ በመሆኑም የትግራይ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ለኤርትራ ህዝብ ያለው ወንድማዊ አድናቆት ከፍ ያለ መሆኑን መግለፅ ይፈልጋል፡፡
የኢትዮ-ኤርትራ ሁኔታ በዘላቂነት ለመፍታት በሚደረገው ሁሉአቀፍ ጥረት የትግራይ ክልላዊ መንግስት እና የትግራይ ህዝብ ከኤርትራ ህዝብ ጎን እንደሚቆሙ እያረጋገጡ የኢትዮጵያና የኤርትራ ህዝቦችም የተጀመረውን ሰላም የማረጋገጥ ስራ ይበልጥ ለማጠናከር በአጭር ጊዜ ውስጥ ቀጥተኛ የሆነ የህዝብ ለህዝብ ግንኙነት በመጀመር ወንድማማችነታቸውንና ወዳጅነታቸውን እንዲያጠናክሩ ጥሪውን ያቀርባል፡፡
የትግራይ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ
ሐምሌ 02 ቀን 2010ዓ.ም
መቐለ
Filed in: Amharic