>

የትግራይ ክልል የወንጀለኞች ምሽግነቷን አረጋገጠች !!! (ቬሮኒካ መላኩ)

የትግራይ ክልል የወንጀለኞች ምሽግነቷን አረጋገጠች !!!
ቬሮኒካ መላኩ
የትግራይ ክልል  የአገርን መሪ ለመግደል ሴራ የጠነሰሰውን ጀነራል ተክለብርሃን ተክለአረጋይ አሳልፌ አልሰጥም ብሎ አሻፈረኝ ብሏል።
እንደት ያለ ድፍረት ነው። የአንድን አገር መሪን ለመግደል የሞከረ ወንጀለኛ እንኳን አንድ የፌደራሉ አባል የሆነ ክልል ይቅርና ማንኛውም የአለም አገር በኤክስትራድሽን ህግ መሰረት ወድያውኑ አሳልፎ ይሰጣል።
ሲጀመር ይሄን አይነት ወንጀል ጁሪስድክሽኑ የክልሎች ሳይሆን የፌደራል ስለሆነ መንግስት ለመከላከያ ወይም ለፌደራል ፖሊስ “ጉሮሮውን አንቃችሁ አምጡት!”  ብሎ ቀጭን ትእዛዝ በመስጠት በሰአታት ውስጥ አዲስአበባ ማምጣት ይችላል ።
ፌደራል መንግስት ቀላሉን መፍትሄ ካልፈለገና እና እነደብረፂዮንም ትእዛዝ መቀበል አሻፈረኝ ካሉ መፍትሄው ቀላል ነው ።
1~ ፌደራል መንግስት ለትግራይ ክልል የመደበውን በጀት እንዳይንቀሳቀስ  ማገድ ።
2~ ወደ ትግራይ የሚገቡና የሚወጡ ማንኛውንም የመገናኛ ፣የቴሌ እና ሌሎች አውታሮችን ብሎክ ማድረግ።በተጨማሪም  ራያ ላይና ጎንደር ላይ ኬላ መወጠር ።
ከዛ በኋላ እነ ሊቀወሲብ ደብረፂዮን  አንድ ወንጀለኛ ከ3 ሚሊዮን ህዝብ ከበለጠባቸው የምናየው ይሆናል።
Filed in: Amharic