>

አንዳርጋቸው እንዲፈታ ተወስኗል ፤ የጣሉት ሁሉ ወድቀው እርሱ ተነስቷል!!! (ቬሮኒካ መላኩ)

 
ፖለቲካ በባህሪው ተለዋዋጭ ነው። የአገራችን  ፖለቲካ እንደዚህ  እንደምንመለከተው እየሆነ ነው ።  ግልብጥብጡ  እየወጣ አሳሪው ታሳሪ እየሆነ ነው።  አንዳርጋቸው እንዲፈታ ተወስኗል ። ነገ ይፈታል ብለን እንጠብቃለን።
አንዲአርጋቸውን በማፈን ሂደት ውስጥ የተሳተፉ አገሮችና ሰዎች ዛሬ  ያኔ እንደነበሩት አይደሉም።
1 ~ አንዳርጋቸውን በማፈን  ሴራ ውስጥ  ዋና አገር የነበረችው የመን   በሰማይ በሚወነጨፍ ሚሳዬልና  በሚወረወር ቦምብ  ፈራርሳና ተደረማምሳ  የድንጋይ  ዘመን አገር ሆናለች።
2~ አንዳርጋቸውን በማሳፈን  ሴራ ከፍተኛውን ሚና የተጫወተው የየመኑ ፕሬዚደንት የነበረው አሊ አብደላ ሳልህ በሁቲ አማፂያን የራስ ቅሉ በጥይት እንደ ዱባ ተፈልጦ ሲሞት በቴሌቪዥን መስኮት  በአይናችን  በብሌኑ አይተናል።
3~ የመን  ሰንአ አለምአቀፍ አውሮፕላን ተርሚናል ውስጥ የታፈነውን  አንዳርጋቸው ፅጌን የራሱን ቻርተር የግል አውሮፕላን ልኮ አስመጥቶ ማእከላዊ እንዲሰቃይ ያደረገው ሼህ መሀመድ አላሙዲን በተራው ሳኡዲ አረቢያ ውስጥ ታስሯል ። ቢዝነሱ እየከሰረ ካምፓኒው እየተዘጋ ከአለም ሀብታሞች ስም ዝርዝር ውስጥ ተፍቋል።
4~ አንዳርጋቸውን በማሳፈን ውስጥ ከ20 ሚሊዮን ዶላር በላይና  አዲስ አበባ የሚገኘውን የትምባሆ ፋብሪካ ለየመን ባለሀብቶች በነፃ የሰጠው የደህንነት ምክትል ሃላፊ የነበረው ወልደሙካኤል በሙስና ሰበብ ታስሮ ቃልቲ  ይገኛል።
አንዳርጋቸው ፅጌ ዛሬ የኢትዮጵያ ህዝቦች በተለይም የአማራ ፋኖና የኦሮሞ ቄሮዎች ታግለው ባመጡት አጠቃላይ ፖለቲካዊ ትግል ነፃነቱን ሊያገኝ ነው።
” ለክፉና ለአመንዝራ ትውልድ ምልክት አላሳየውም፡፡ እንዲሁ አጠፋዋለሁ!”  እንደሚለው  ፍካሬ – ኢየሱስ ክፉና አመንዝራ የሆኑትና የታሪክ ጎርፍ እያግበሰበሰ ያመጣብን ወያኔዎች  ምልክት ሳያዩ እየጠፉ ነው።
ቦ ጊዜ ለኩሉ  !!
Filed in: Amharic