>

የትግሬ ንብረት ተንካ እንጂ- አማራው ኦሮሞው ጋምቤላው...ለምን ይገደላል ያለ አለ? ይሄስ ያኗኑረናል? (ምስጋናው እንዱ አለም)

የህወሀት ጀሌዎች ጠሚ አብይ በትግርኛ መናገሩን ተከትሎ አማሮች ለምን በትግርኛ ተናገረ ብለው እንደተቀየሙ አይነት ነገር ያሰራጫሉ፡፡ በጣም የተሳሳተ እና አሳፋሪ ጸረ አማራ ዘመቻ ነው፡፡ አንድም አማራ ለምን በትግርኛ ተናገረ ያለ የለም፤ ሊልም አይችልም፤ ሊልም አይገባም፡፡ አማርኛ ተናጋሪዎች ግን እንደዛ አይነት ነገር ሳይናገሩ አይቀሩም፡፡ ማለትም ከህወሀት ካድሬዎች ውጭ ያሉት አማርኛ ተናጋሪዎች፡፡ ያው ህወሀቶችም አማርኛ ተናጋሪ ስለሆኑ በአንድ ጎናቸው፡፡ እናም አማርኛ ተናጋሪዎች አብይ “ህገ-መንግስቱን” ጥሷል፤ በህገ-መንግስቱ መሰረት በአማርኛ ነበር መናገር የሚገባው ብለዋል፡፡ ትክክል ሊሆኑ ይችላሉ፤ ላይሆኑም ይችላሉ፡፡ እኛ አማሮች አያገባንም፡፡ ምክንያቱም መጀመሪያም ህገ-መንግስቱ እኛን የማይመለከት ነው እያልን ያለነው፡፡ ስለዚህ በአማርኛ ተናገረ በትግርኛ ወይም በኦሮምኛ እኛን አያባንም፡፡
በነገራችን ላይ አማርኛ ስትናገሩ ለአማራ እንደጠቀማችሁ ማሰባችሁን ማቆም አለባችሁ፡፡ አማርኛ በመናገራችሁ እናንተ ናችሁ የምትጠቀሙት፡፡ አማራ ቤሳ ቢስቲን አያገኝም፡፡ እንግዲያውማ አንድ “መሪ” የሚያስተዳድረውን ህዝብ ቋንቋ መናገሩ ተገቢ ነው፤ ስሜታዊ ትስስር (Emotional attachment) ይፈጥራል፡፡ ስለዚህ አብይ በኦሮምኛም፣ በትግርኛም መናገሩ ተገቢ ነው፡፡ ተገቢ ያልሆነው ነገር ግን የተናገረው ንግግር ይዘት ነው፡፡ ንግግሩን እንኳን በትግርኛ በ”ልሳንም” ቢናገረው ትክክል ካልሆነ አልሆነም ነው፡፡ እናም የህወሀት ካድሬዎች አብይን ትግርኛ ማናገር ብቻ ሳይሆን ትግሬ ማድረግ ትችላላችሁ፡፡ የእኛ ጉዳይ አይደለም፡፡ የእኛ ጉዳይ ወልቃይትን መልሱ፤ ከዛም ባሻገር እኔ እኔ ብቻ አትበሉ ነው፡፡ እውን እዛ መቀሌ ላይ ሲናገሩ የነበሩት ሰዎች እና ሌሎች ካድሬዎች የሚያስተጋቡት አብሮ የሚያኖር ነው? እዛ ስብሰባ ላይ የተናገሩት እና መላ ካድሬዎች ትግሬ ለምን ንብረቱ ተቃጠለ፣ ለምን ተነካ ነው እንጅ አማራስ ለምን ይገደላል፤ ኦሮሞስ፣ ኮንሶስ፣ ጌዴዎስ ለምን ይገደላል  አላሉም፡፡ እንዲህ አይነቱ ጭፍን ያለና ራስ ወዳድ ነገር ነው አብሮ የማያኗኑረው፡፡ አሁንም ይደገም፡- አንድስ እንኳ አማራና ሌሎች ለምን ተገደሉ የሚል አለመገኘቱ አንድ አገርነትን፣ አንድ ህዝብነትን ያመለክታል ወይ? አእምሮ ላለው እና በጥሞና ለሚያየው በጣም አሳዛኝ ነገር ነው፡፡ ለማጠቃለልም- ለወደፊቱ የአማራን እና የአማርኛ ተናጋሪን አጀንዳ ለይታችሁ ተንቀሳቀሱ፡፡ አማርኛ ተናጋሪው በሚያነሳው አጀንዳ ሁላ እየዘለላችሁ አማራ አትበሉ፡፡
Filed in: Amharic