>

የመልዕክት ደወል ለኢትዮጵያ የሀገር መከላከያ ሰራዊት በሙሉ?! (አሰፋ ኢትዮጵያ)

  የትግራይ ህዝብ  የኦረሞን  ህዝብ  በየጎዳናው  የሚገድለው  የሚያሠድደው  በእራሱ  ሀይልና  ብርታት  ተማምኖ  አይደለም  የመከላከ  ሰራዊቱን  ስለያዘ  ብቻ  እንጂ።  የትግራይ  ህዝብ  አማራውን  በግፍ  የሚያስገድለው  የአማራን  መሬት  ከራያ  አዘቦ  እስከ እራያ  መኾኒ  ከሁመራ  እስከ  ወልቃይት  ጠገደ  በመጠቅለል  ወደ  ትግራይ  ክልል  ለማካለል  ሰፍ  ያለው  በእራሱ  ሀይልና  ብርታት  ተማምኖ  አይደለም  የመከላከያ  ሰራዊቱን  ስለያዘ  ብቻ  እንጂ።  ለመሆኑ  የኢትዮጵያ  መከላከያ  ሰራዊት  ተጠሪነቱ  ለኢትዮጵያ  ህዝብ  ነው  ወይስ  ለትግራይ ለትግራይ  ህዝብ?  አመታዊ  ወጪውንስ  የሚሸፍነው  የኢትዮጵያ ህዝብ  ነው  ወይስ  የዘመናችን  ወርቅ  ትግራይ?  እየተገደለና  እየተበደለ  ያለው  የኢትዮጵያ  ህዝብ  ሁኖ  ሳለ  በዚሁ  ተበዳይ  ህዝብ  ላይ  የጂምላ  ግዲያና  ስቃይ  ሊፈፀምበት  የቻለው  የትግራይ  ወንበደወች  የመከላከያ  ሰራዊቱንና  ደህንነቱን ስለተቆጣጠሩት  ብቻ  ነው።  ይህንንም  ገዳይና  ህዝብን  የሚያሸብር  አፋኝ  ስርዓት  ከእኩይ  ተግባሩ  ሊያስቆመው  የሚችለው  የሀገር  መከላከያ ሰራዊቱ  ከሀገሪቱ  ተጨባጭ እውነታ  በመነሳት  በኢትዮጵያዊ  ወገኖቹ  ላይ  የሚፈፀምባቸውን  ግፍና  የጂምላ  ግዲያ  በትክክል  በመረዳት  በቃ  ሲለው  ብቻ  ነው።  የአንድ  ሀገር  ህዝብ  በአናሳ የስልጣን  ጥመኞችና  ዘራፊወች  የሚፈፀምበትን  ግፍና  በደል  ለማሰማት  ወደ  አደባባይ  በወጣ  ቁጥር  መልሱ  ጥይት  በሆነበት  ሰዓት  ያከህዝብ  አብራክ  የወጣ  የህዝብ  ሰራዊት  የወገኖቹ  ደም  ከውሃ  እረክሶ  ሲፈስ  እናትና  አባቱ  እህትና  ወንድሞቹ  በቀሄያቸው  የመኖር  መብታቸውን  ተነፍገው  ከሀገር  ሲሰደዱ  ለሀገሩ  ህዝብ  ተዚህ  የከፋ  ጥላት  ይመጣል  ብሎ  ነው  የኢትዮጵያ  መከላከያ  ሰራዊት  የወገኖቹን  ደም  በዝምታ  ለመመልከት  የተገደደው?
የኢትዮጵያ  መከላከያ  ሰራዊት  ሆይ  ልትገነዘበው  የሚገባህ  ጉዳይ  ለማስታወስ  ያክል፤  ለኢትዮጵያ  ከኢጣሊያን  የበለጠ  ወራሪ  አልነበራትም።  ግን  ጣሊያን  ጥፍራችንን  በፔንዛ  አልነቀለም፣  ብልቶቻችንን  አላኮላሸም፤  ዘርንና ብሄርን  እየመረጠና  እየለየ  አልገደለንም፤  ልጁን  ገድሎ  እናቲቱን  እልጅሺ  እሬሳ  ላይ ቁመሺ  ደልቂበት  ጨፍሪበት  አላለም  በባርነት  ልግዛችሁ  አለን  እንጂ  ከሀገራችሁ  ውጡ  ብሎ  አላሳደደንም፤  የትግሬው  ወንበዴ  ቡድን  ወያኔ  ግን  ጥፍራችንን  ነቅሏል  ብልታችንን  አኮላሺቷል  ልጇን  የገደለባትን እናት  እልጇ  አስክሬን  ላይ  አስደልቋታል  አስጨፍሯታል፡  በዘርና  በቋንቋ  እየለየ  እረሺኖናል፡  በመቶ  ሺዎች  የሚቆጠሩትን  ከሀገር  አሰድዷል  ጣሊያን  ያልፈፀመብንን  ግፍና  በደል  ፈፅሞብናል  ታዲያ  በእንድህ  አይነቱ  አረመኔ  ላይ  እርምጃ ያልወሰድክ  ከእንድህ  አይነቱ  መከራ  ህዝብን  ያልተከላከልክ  በምን  መመዘኒያ  ነው  የህዝብና  የሀገር  መከላከያ  ልትሆን  የምትችለው?  ዛሬ እኮ  ወደ  አምሳ  ሺህ  50ሺህ  ኦረሞ  ወደ  ኬኒያ  የተሰደደው  የውጭ  ጥላትን  ፈርቶ  አይደለም  የትግራይ  መለዮ  ለባሾች  በወሰዱበት  የጭካኔ  እርምጃ  ደራሺ  እና  ተቆርቋሪ  በማጣቱ  ከጥላት  ይጠብቀኛል  ያለው  የመከላከያ  ሰራዊት  ከጎኑ  ባለመሆኑ  ነው  ተስፋው  ተሟጦ  ወደ  ባዕድ ሀገር  የተሰደደው።  አሁንም    ህዝባችን   በድብቅ  በትግራይ  ተወላጆች  እየተሰለሉ  ውስጥ  ውስጡን  በመታነቅ  ነው።  የኢትዮጵያ  ህዝብ  መብቱ  በመረገጡና  ድምፁ  በመታፈኑ  የታፈነውን  ድምፁን  ለማሰማት  ወደ  አደባይ  በተደጋጋሚ  የወጣው።  መልሱ  ግን  ጥይት  ብቻ  ከመሆን  አላለፈም።  ለዛም  ነው  ለመብቱ  የጮኸ  ህዝብ  አሸባሪና ሁከት  ፈጣሪ  እየተባለ  በወያኔ  እየተፈረጀ  በተደጋጋሚ  ሲገደል  የነበረው።  ግዲያውም  እያየለ  በመምጣቱ  በአስር  ሺህዎች  የሚቆጠሩ  ከሀገር  ውጭ  የተሰደዱት።  ዛሬም  በትግራይ  ሰላዮች  እየታፈኑ  የሚታሰሩ  እንዳሉ  ሁሉ  አገር  ጥለው  የሚሰደዱትም  ብዙ  ናቸው።  ህዝብ  ሲገደል  ህዝብ  ሲሰደድ  ከህዝብ  የወጣ  የሀገር  መከላከያ  ሰራዊት  ወደየት እንደተሰወረ  አይታወቅም።    የሚታወቀው  የመከላከያ ሰራዊት  ልብስ  የለበሱ  ወንበዴወች  ህዝብን  ሲገድሉ  እና ሲያሳድዱ  ብቻ  ነው።  የአማራው ህዝብ  መሬቱ  በመዘረፉ  እና  በመወረሩ  ምክናየት  ጥያቄ  ስላነሳ  ብቻ  በትግራይ  አጋዚ  ወታደር  ህይወቱን  አቷል።  መሬቱ በመዘረፉ  እና  ከቀሄው  በመፈናቀሉ  ብሶቱን  ለማሰማት  ወደ  አደባባይ  የወጣ  ህዝብ  የሻዕቢያ  ተላላኪ  እየተባለ  በውሸት  ፍረጃ  ግማሹ  ሲገደል  ከፊሉ  ደግሞ  ታስሯል።  በመታሰሩም  ጥፍሩ  ተነቅሏል  ብልቱ  ተኮላሺቷል።  የኢትዮጵያ  መከላከያ  ሰራዊት  ሆይ  ተመልከት  ይህንን  የተጨቆነና  የታፈነ  ህዝብ  ነው  ወያኔ  አሸባሪ  ሁከት  ፈጣሪ  የሻዕቢያ  ተላላኪ  እያለ  አንተን  የሚሰብክህና  ወገንህን  እንዳትታደግና  ፈጥነህ  እንዳትደርስለት  በውሸት  ፕሮቡጋንዳው  አዕምሮህን  ያወረው።  ዛሬ  ብዙወቹ  ኦረሞ  ወገኖችህ  በሚፈፀምባቸው  ግፍና  በደል  አሰቃቂ  ግዲያ  ምክናየት  አገር  እንደሌላቸው  በኬኒያ  ጫካ  ፀሀይና  ንፋስ  ይፈራረቅባቸዋል።  አንተ  ከእነሱ  አብራክ  የወጣኸውም  ያደረግከው  ቅንጣት  ነገር የለም።  ከኦረሚያ  ኦረሞ  ይሰደዳል።  ትግራይ ግን  በኦረሚያ  የፈለገውን  ሃሳብ  ያራምዳል  ትግራ  ከትግራ  እየፈለሰና  እየተሰደደ  በኦረሚያ  ክልል  የበላይነትን  ይዞ  እንደፈለው  ሃሳቡን  ያራምዳል  የፈለገውንም  ያደርጋል።  በኦረሚያ  በሺህ  የሚቆጠሩ  ኦረሞወች  በአጋዚ  ወታደር  ሲገደሉ  አንድ  የትግራይ  ተወላጂ  መሞት  ይቅርና  አልቆሰለም  ይደርማል። ዛሬ  በኦረሚያ  ክልል  አዛዡ  ትግሬ  ነው  ባለሀብቱ  ትግሬ  ነው  ባለቤቱ  የኦረሞ  ህዝብ ግን  ለክልሉ ያተረፈው  አሸባሪ  የሚባል  ስም ብቻ  ነው።  የአማራው  ህዝብ  በአማራ  መሬት  ማዘዝ  ይቅርና  ሰለ  መሬቱ  ጉዳይ  ታነሳ  የሻዕቢያ  ተላላኪ  ነው  ሺብር ፈጣሪ  ነው  እየተባለ  በትግራይ  ጀኔራሎች  የማሸማቀቂያ  ቃላት  እየተፈረጀ  ወደ እስር  ቤት  ይወረወራል።  እውነታው  ግን  ወያኔ  ከኢትዮጵያ  መሬት  እየቆረሰ  ለሻዕቢያ  ሲሰጥና  ሲያድል  ነው  የምናየው።  ለሱዳንም  በመተማና  በሁመራ  የአማራ  ክልል  የሚገኙ  የኢትዮጵያ  ጠፍ  መሬቶችን  ሲሸጥና  ሢዋዋል  ነው  የምንሰማው።  የአማራ  ህዝብ  ደግሞ  ይህንን  አገር  የመሸጥ  የወያኔንን  አላማ  በፅኑ  ይቃወማል  እየተቃወመም  ነው።  ይህንን ህዝብ  ነው እንግድህ  የትግራይ  ሹማምንቶችና  ጀኔራሎች  በተቆጣጠሩት  የመከላከያ  ሀይል  በጂምላ  የሚያስረሺኑት።  የኢትዮጵያ  መከላከያ  ሰራዊት  ሆይ  ያለፈው  አልፏል  አይመለስም  ስለሆነውም ነገር  ሁሉ  የኢትዮጵያ  ህዝብ  ተጠያቂ  ያደረገው  የትግራይን  ወንበደ  ቡድን  ወያኔን  እንጂ  አንተን  ከአብራኩ  የወጣኸውን  ውድ  ልጁን  አይደለም  ስለሆነም  እውነታውን  በመረዳት  በወገኖችህ  ላይ   የታወጀውን  የአፈና  አገዛዝ  በቃህ ልትልለት  ይገባል።  እናት  እልጇ  እሬሳ  ላይ  ጨፍሪ  ከመባል  ውጭ  ምን  አይነት  ግፍና  ጭካኔ  እስከሚመጣ  ነው  የምትጠብቀው?  በፍፁም  እንግድህ  መጠበቅ  የለብህም።   የኢትዮጵያ  መከላከያ  ሰራዊት  ሆይ  ላሳውቅ  የሚገባው  ነገር  ከላይ  የዘረዘርኳቸውን  የተፈፀሙ  ወንጀሎች  ጨምሮ  በኦረሚያ ክልል  ሞያሌ  ከተማ  የተፈፀመውን  ተግባር  ወያኔ  ያላከከውና  ያመሃኘው  በአንተው  ላይ  ነው።  የወያኔን  ተንኮልና  ደባ  በደንብ የተረዳው  ህዝብ  ግን  ተጠያቂ  ያደረገው  አንተን ሳይሆን  እራሱን  ወያኔንና  የትግራይ  ጀኔራሎችን  አዛዦችን  ነው።  ያልተማረውና  ያልሰለጠነው  ወገንህ  እየሞተና  እየተሰደደ  ለአንተ  ነፃነት  ጭምር  ሲታገል  በእውነቱ  ምን  ሊሰማህ  እንደሚችል  መግለፅ  ይከብደኛል።  የዚህን  ህዝብ  ወለታ  መመለስ  የምትችለው  አሸባሪውን  የወያኔ  ስርዓት  በቃ  ብለህ  ከህዝቡ ጎን ስትቆም  ብቻ  ነው።
ድልን  እስከሚጨብጥ  የኢትዮጵያ  ህዝብ  ከጀመረው  ትግል  ወደ  ሗላ  አይልም!!
ይህ  እውነታ  በአጋጣሚ  የደረሰህ  የኢትዮጵያ  መከላከያ  ሰራዊት  አንተ  ብቻ  አይደለህም  ማወቅ ያለብህ  ይህንን  የሰማኸውን  እውነታ  ለሌሎች  ባልደረቦችህም  ጭምር  ማሳወቅ  እንዳለብህ  ላሳስብህ  እወዳለሁ።
ይህንን  ነፃነት  ናፋቂ  ህዝብ  የምትተባበርበት  ጊዜው  አሁን  ነው።
ድል ለመላው  ኢትዮጵያ  ህዝብ!!
Filed in: Amharic