>
5:13 pm - Thursday April 18, 3602

የኢትዮጵያ ሕጻናት ሰቆቃ! (አቻምየለህ ታምሩ)

እነዚህ ከታች የምትመለከቷቸው ሕጻናት የትግራይ ወታደሮችን  ጥይት አምልጠው  በጎረቤት አገር ኬንያ ስደተኛ የሆኑ የሞያሌ እንቦቀቅላዎች ናቸው። የወያኔዋ  ኢትዮጵያ እንዲህ  ሕጻናት ነፍሳቸውን ለማዳን የጎረቤት አገር  ድንበር አቋርጠው የሚሰደዱባት አገር ሆናለች።

የወያኔ ዘመን ሕጻናት የወላጆቻቸው ድህነትና ስደት  የወለደው ርሃብ በገረፋቸው ቁጥር ዕንባ ሲያመነጩ የሚውሉት አይኖቻቸው ዘወትር ቀይ ሽንኩርት መስለውና ደፍርሰው የትራኮማ መፈልፈያ ሆነዋል። በገጠሩ የአገራችን  ክፍል የሚገኙ ሕጻናትን ለተመለከተ  የእንባ መጉረፊያ የሆኑት ጉንጮቻቸው ዘወትር የበቆሎ ቡሆ የፈሰሰባቸው መስለው ከመታየታቸው በላይ አልፎ አልፎ ከወጡባቸው ጭርቶች ጋር ፊታቸውን ፍጹም ዓመድ አልብሰውት ይታያል። በየቀኑ የሚገርፋቸው የርሃብ አለንጋ ከሰውነት ውጭ ስላደረጋቸውና የመልካቸው ውበት ስለተለወጠ፡ የተገተነ መጋፊያ ከሚመስለው ፊተ ገጻቸው ላይ ተገትሮ የሚታየው አፍንጫቸው የተመለመ ጎን አጥንት መስሎ ከውበት ወደ አስቀያሚነት መለወጡን ይመሰክራል። ሐር የሚመስለው ላዛ ፀጉራቸው በዱቄትና በአቧራ ከመታፈኑ በላይ የተፈጨ ጥሬ ጨው የመሰለ ቅማጭ ውጦት ይገኛል።
የኢትዮጵያ ሕጻናት  ይህ ሁሉ የተፈጸመባቸው ግፍና መከራ አልበቃ ብሏቸው ሰው ለማጥቃት የሰለጠኑ የትግራይ ወታደሮች እየተሰማሩ ከጓደኞቻቸው ጋር ሊጫወጡ ከቤታቸው  የወጡ የድሃ ልጆችን  እየረሸኑ እንደወጡ እያስቀሯቸው  ይገኛሉ። እነዚህ  ከታች የሚታዩት የሞያሌ ህጻናት  እግሬ አውጭኝ ብለው ድንበር ጥሰው ወደ ጎረቤት አገር ባይሰደዱ ኖሮ   እንደ ወልድያና  ነቀምት ሕጻናት በትግራይ ወታደሮች የሚረሸኑ ነበሩ።
የኢትዮጵያ ሕጻናት በድህነት አጥንታቸው መቅረቱ [stunted መሆናቸው] ሳያንስ  አስር አመት ሳይደፍኑ  በትግራይ ወታደሮች እየተረሸኑ ወላጅ ሕጻን ቀባሪ ሆኖ  የቤተሰብ ተስፋ እየተቀጨ ያለው   በእኛ መከራ ላይ ተደላድለው የመሬት ዝርፊያና የጮማ ቁንጣን፤ የቮድካና የውስኪ ሞቅታ የሚያሰቃያቸው የተከዜ ማዶ ባለጊዚዎች ምቾታቸና ዘረፋቸው እንዳይጓደል ነው።
Filed in: Amharic