>
5:13 pm - Sunday April 19, 7096

እነዚህ ሰዎች እኮ አብደዋል!! (ግርማ ሰይፉ ማሩ)

ወዳጆቼ በአገራችን ያለው ገዢ “አብዮታዊው ዴሞክራሲያዊው ግንባር (አዴግ)” እብድ ነው ብሎናል ወዳጄ አቤ ቶክቻው፡፡ እኔም ተሰማምቻለሁ፡፡ ለዕብደታቸው መገለጫ ይሆን ዘንድ ምሣሌዎችን አቅርቧል፡፡ ይህ እብደቱ ግን የከረመ እንጂ አዲሰ አይደለም፡፡ በትግራይ ያሉትን ታጋዮች በተኙበት በገደለበት ወቅት ይጀምራል፡፡ መቼም ሁሌም በማንበርከክ እሳቤ ውስጥ ያለን ድርጅት የጋራ አሸናፊነትን ሊቀበል አይችለም፡፡ የፖለቲካ ምዕዳር ለማስፋት ዋንኛው መንገድ ብዙ ተሸናፊዎችን በመሰብሰብ ሳይሆን፤ እጀግ ብዙ ቀና ብለው የሚሄዱ ዜጎችን በማፍራት ነው፡፡ አዴግ ያልገባው ነገር፤ የአንበረከካቸው ወይም ያሸነፋቸው የመሰሉት ሰዎች ሁሉ፣ አድፍጠው ይጠብቁታል እንጂ አጎንብሰው አይቀሩም፡፡ የፕሮፌሰር መስፍንን እንዘጭ እንቦጭ ማንበብ ይጠቅማል ለዚህ ጉዳይ፡፡ ሰለ አድፋጭነት፡፡ አድፋጮች የመጨረሻው ቀን መቃረቡን ሲያውቁ እንደ ንብ መንጋ ይወሩታል፡፡ ቀና ብለው የሚሄዱ በራሳቸው የሚተማመኑት ግን ዛሬ ያለማጎንበሳቸው ሳይሆን፤ ነገም ለተፈጠረው ሁሉ የይቅርታ ልብ ይኖራቸዋል፡፡ አንዱዓለም፣ እስክንድር፣ ናትናኤል፣ ወዘተ ይህን ሊያደርጉ የሚችሉ እንደሆነ አምናለሁ፡፡ ለዚህም ነው ለማጎንበስም እንቢ የሚሉት፡፡ ማጎንበስ ቢፈልጉ፤ ለጥቅም ቢገዙ ቀድሞውንስ እዚህ ደረጃ ምን ያዳርሳቸው ነበር፡፡ ይህን መከራ በክብር የተቀበሉት፣ እየተቀበሉ የሚቀጥሉትም ላለማጎንበስ ነው፡፡ አዴግ ዛሬም ኳሱ በእጁ መሆኑን ማን እንደሚነግረው ባለውቅም በዚህች አገር የፖለቲካ ምዕዳር መስፋት ሁሉም የሚያገባው መሆኑን ማሳየት ይጠበቅበታል፡፡

ገዢያችን አዴግ ለለውጥ ዝግጁ ያለመሆኑን ከሚያሳይበት መግገድ አንዱ በቅርቡ የምርጫ ቦርድ አድርጎ የሾማቸው ሰዎች ናቸው፡፡ በስታትሰቲክስ ፅ/ቤት መረጃ በተሳሳተ መንገድ በማቀናበር እድሜ ዘመናቸውን ገዢውን ፓርቲ ሲያገለገሉ የከረሙ ሴት፣ አሁን ደግሞ ገለልተኛ ሆነው ምርጫ ይመራሉ ብለን እንድናምን ይፈልጋሉ፡፡ እኚህ ሴት በእውነት ለመናገር ከየትም አገር በተለይ በቁጥር እንኳን እንዳንተማመን ያደረገን መስሪያ ቤት በፍፁም አድርባይነት ያገለገሉ ብቻ ሳይሆን ለዚህ ውለታቸው በአምባሳደርነት ሹመት ያገኙ ናቸው፡፡ ይህን ስናሰበው አዴግ ለመታረም ዝግጁ አይለም እንላለን፡፡ የፖለቲካ ምዕዳር ይስፋ ሲባል ይህን የበሰበሰ ምርጫ ቦርድ የሚባል ተቋም መፍርስ አለበት ማለታችን ጭምር ነው፡፡ ይህ መስሪያ ቤት መታደስ አይደለም መፍረስ የሚበቃው አይመሰለኝም፡፡

ለማንኛውም አዴግ ልብ ቢገዛ ጥሩ ነው፡፡ አሁን ቀና ብሎ የሚሄደው እየበዛ ነው፡፡ የሚሊዮኖች ድምፅ ለነፃነት እያስተጋባ ነው፡፡ ጎርፎ ሆኖ ጠራርጎ ሳይወስደው በዚህ ህገወጥ በሆነ “የፀረ-ሸብር ህግ” ሰበብ የተሳሩ ዜጎችን ያለምንም ቅድመ ሁኔታ መፍታት፤ የፖለቲካ ምዕዳሩን ከሌሎች ሀይሎች ጋር በመተባበር ለማስተካከል አሳታፊ መልካም እርምጃ ከመውሰድ ይልቅ በተናጥል የሚደረግ ህገ ወጥ ሹመቶችን የምርጫ ቦርድ ዓይነቱን ማቆም ባፋጣን ለአገራው መግባባት የሚረዳ ሁሉንም ያገባኛል የሚሉ ሀይሎች የሚያሳትፍ ጉባዔ መጥራት ይኖርበታል፡፡ ጉባዔውን ፋና እንደማይጠራው እምነት አለኝ፡፡ እነዚህ ሰዎች እኮ አብደዋል የምንለው ለዚህ ነው፡፡ መፍትሔ የሚፈልጉትን ከጥፋት ቦታ ነው፡፡

Filed in: Amharic